ይህ ባህል ደሮ የልጃገረድ፣ የሙሽሪት ባህል ብቻ ነበር ። አሁን ወንዱ ሙሽራም ሴቷን መፎካከር ጀምሯል ።
ድሮ ድሮ አንዲት ልጃገረድ ከሰርጓ አንድ ወር በፊት ጥፍሯ ይቆረጥ ነበር ። ለምን የሚለው ብዙ ታሪክ አለው፣ እዚያ አልገባም ።
ከዚያም ለ1 ወር ማታ ማታ ሚዜዎችና ጓገኞችዋ ቤቷ እየዘፈኑ የጥፍር ግብዣ ይበላ ነበር ። ዘመዶቿ የሆኑ ሁሉ ምግብ እየደገሱ ያመጡና በየማታው የጥፍር ይዘፈን ይበላ ነበር ።
ከዚያም ሰርጓ እሁድ ሆኖ 3 ቀን በፊት እጅና እግሮቹዋ ላይ እንሾሽላ የሚታሰርላት እለት ነበር ። ያ እለት መላ ዘመድ አዝማዶችዋ ቤቷ ተሰብስበው የእንሾሽላ የቤተሰብ መሰነባበቻ በዓል ተደርጎላት እንሶስላ ይታሰርላት ነበር ። ቀኑ በጣም ሆድ የሚያባባ መሰነባበቻ የነበረ ሲሆን ዘፈን የሚያወርዱላት እናቷ፣ አባቷ፣ አያቶቿ ና አስክስቶቿ ነበሩ ።
ይህ ባህል ቀዝቀዝ ብሎ ከኖረ በኋላ ባለፉት 15 አመታት እጅግ እጅግ በሚያስደንቅ ሁኔታ የገነነ መላ ጉራጌን ክርስቲያን ሙስሊም ሳይል ስልቴን ጨምሮ የጉራጌ ልጃገረዶች እየነቀነቀ ይገኛል ።
በዚህ ልክ የመግነኑ ምክኛት ሴቶችን እጅክ ከፍ የሚያደርግ፣ የዘር ግንድ ፣ የቤተሰብ ጌታ መሆናቸውን ስለሚያገን ነው ።
ዛሬ ላይ እንሾሽላ ላንዲት ሙሽራ ከሰርጓል በላይ ያማረ ነገር እየሆነ ነው!
ይህ ባህል ወደፊት የሌሎች ብሄረ ሰብ ልጃገረዶች እያማሩበት ቢመጡ አልደነቅም!
በዚህ የአዲስ አመት ዋዜማ እንሾሽላን አስተዋውቃችኋለሁ !
የኬር አክራሚ ለኩልምኛ !!!