ክልል ከክልል ያለው ግንኙነት በትብብር እና ህግን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል፡- ሰላም ሚኒስቴር
Posted: 18 Jun 2023, 09:52
ክልል ከክልል ያለው ግንኙነት በትብብር እና ህግን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል፡- ሰላም ሚኒስቴር
***************************************
ክልል ከክልል ያለው ግንኙነት በትብብር እና ህግን መሠረት ያደረገ መሆን እንዳለበት የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ስዩም መስፍን ተናገሩ።
የሰላም ሚኒስቴር ከድሬዳዋ አስተዳደር ፍትህና የህግ ጉዳዮች ቢሮ ጋር በመተባበር የምሥራቅ ኢትዮጵያ አጎራባች ክልሎች እና ከተማ አስተዳር የጋራ የውይይት መድረክ አካሂዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ፍትህ እና የህግ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አብደላ በከር፣ ሰላማችንን ሁሌም ልንከባከበው ይገባል፤ ስለ ሰላም የምንሰራው ግጭት እና ብጥብጥ ውስጥ ከገባን በኋላ መሆን የለበትም ብለዋል።
ሁለንተናዊ እና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የአጎራባች ክልሎች የእርስ በእርስ ግንኙነት እና መናበብ በእጅጉ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
በመድረኩ ላይ በፌዴራሊዝም፣ በመንግሥታት ግንኙነት ጽንስ ሀሳብ እና የመንግሥታት ግንኙነት ሥርዓት የተመለከቱ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የሰላም ሚኒስቴር የፌዴራሊዝም እና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ስዩም መስፍን፣ ከመንግስታት ግንኙነት አዋጁ አንዱ የጎንዮሽ ግንኙነት መሆኑን ጠቅሰው፤ ክልል ከክልል ያለው ግንኙነት በትብብርና ህግን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል ብለዋል።
የፌዴራሊዝም ሥርዓት ያለ መንግስታት ግንኙነት ጠንካራ ሊሆን አይችልም ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፣ የመንግሥታት ግንኙነት በደንብ ባለመጠንከሩ ምክንያት ትንንሽ ችግሮች እየሰፋ ብጥብጥ ሲፈጥር ይስተዋላል ብለዋል።
አክለውም፣ በክልሎች መካከል የሚፈጠሩ ግጭቶችን ክልሎች ራሳቸው በሰከነ መንገድ የመፍታት ባህል ሊያጎለብቱ እንደሚገባ ጠቁመው፣ አንዳንድ ክልሎች በዚህ በኩል ብዙ ለውጥ እንዳመጡም መግለጻቸውን ከሰላም ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
***************************************
ክልል ከክልል ያለው ግንኙነት በትብብር እና ህግን መሠረት ያደረገ መሆን እንዳለበት የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ስዩም መስፍን ተናገሩ።
የሰላም ሚኒስቴር ከድሬዳዋ አስተዳደር ፍትህና የህግ ጉዳዮች ቢሮ ጋር በመተባበር የምሥራቅ ኢትዮጵያ አጎራባች ክልሎች እና ከተማ አስተዳር የጋራ የውይይት መድረክ አካሂዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ፍትህ እና የህግ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አብደላ በከር፣ ሰላማችንን ሁሌም ልንከባከበው ይገባል፤ ስለ ሰላም የምንሰራው ግጭት እና ብጥብጥ ውስጥ ከገባን በኋላ መሆን የለበትም ብለዋል።
ሁለንተናዊ እና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የአጎራባች ክልሎች የእርስ በእርስ ግንኙነት እና መናበብ በእጅጉ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
በመድረኩ ላይ በፌዴራሊዝም፣ በመንግሥታት ግንኙነት ጽንስ ሀሳብ እና የመንግሥታት ግንኙነት ሥርዓት የተመለከቱ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የሰላም ሚኒስቴር የፌዴራሊዝም እና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ስዩም መስፍን፣ ከመንግስታት ግንኙነት አዋጁ አንዱ የጎንዮሽ ግንኙነት መሆኑን ጠቅሰው፤ ክልል ከክልል ያለው ግንኙነት በትብብርና ህግን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል ብለዋል።
የፌዴራሊዝም ሥርዓት ያለ መንግስታት ግንኙነት ጠንካራ ሊሆን አይችልም ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፣ የመንግሥታት ግንኙነት በደንብ ባለመጠንከሩ ምክንያት ትንንሽ ችግሮች እየሰፋ ብጥብጥ ሲፈጥር ይስተዋላል ብለዋል።
አክለውም፣ በክልሎች መካከል የሚፈጠሩ ግጭቶችን ክልሎች ራሳቸው በሰከነ መንገድ የመፍታት ባህል ሊያጎለብቱ እንደሚገባ ጠቁመው፣ አንዳንድ ክልሎች በዚህ በኩል ብዙ ለውጥ እንዳመጡም መግለጻቸውን ከሰላም ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
Please wait, video is loading...