ዲያቆን ሳይሆኑ ኤጲስ ቆጶስ ፤ 12ኛ ክፍል ሳይጨርሱ ፒኤችዲ/PhD --> የአቶ ዐብይ አህመድ ኦሮሙማ መንግስት ጥራት እና ብቃት።
Posted: 21 May 2023, 12:45
ዲያቆን ሳይሆኑ ኤጲስ ቆጶስ ፤ 12ኛ ክፍል ሳይጨርሱ ፒኤችዲ/PhD --> የአቶ ዐብይ አህመድ ኦሮሙማ መንግስት ጥራት እና ብቃት።አቶ ዐብይ ቤተክርስቲያን እንደ ቀበሌ ዲያቆን ሁኖ የማያውቁ ልቅምቅም ካድሬዎችን ኤጲስ ቆጶስ እሾማለሁ ብሎ መከራውን እየጨረሰ ነው - ይህ እንደ እርሱ ትምህርት በአቋራጭ ማጅራት መምታቱ ነው። ይህ የሚሆን ከሆነ ምናልባትም ፓትራያርኩን ከህዝብ እንደሚለያቸው እና እንደ ቀድሞ አባ ገብረመድህን (ጳውሎስ) አድርጎ ሊያያቸው ይችላል። አብይ አህመድ ብዙዎችን ከደጋፊ መንጋቸው በመነጠል የዝቅተኛ ስሜት እና የነቀፋ ሰለባ አድርጓቸዋል።