Page 1 of 1

ኢትዮጵያን፥ካለችበት፥ ችግር፥ማውጣት፥ ይቻላል፤

Posted: 17 May 2023, 23:36
by Axumezana
አብይ፥ ላለፉት፥ አምስት፥ አመታት፥ በውጭ፥ በውስጥ፥ ሃይሎችና፥ በራሱ፥ ስህተቶች፥ ውስብስብ፥የተደረገውን፥ የኢትዮጵያ፥ ሁኔታ፥ ለማስተካከል፥ ቢሞክርም፥ችግሩ፥ አልተቀረፈም። እንደተባለው፥ ህገመንግስቱ፥ ላይ፥ የተመረጡ፥ ለውጦችን፥ ወይም፥እገዳዎችን፥
በአስቾካይ፥ አድርጎ፥ በህዝቡ፥ተሳታፊነት፥ አገሪቱን፥ መታደግ፥ ይኖርበታል። በፈረሰ፥ አገር፥ ባለስልጣን፥ መሆን፥ ስለማይቻል፥ የዲሞክራሲ፥መጫወቻ፥ ሜዳውን፥ ለሌሎች፥ ክፍት፥ በማድረግ፥ የሚቀጥለውን፥ምርጫ፥ ዲሞክራስያዊ፥ ማድረጉ፥ አገሪቱን፥ ያረጋጋል። በቅርቡ፥ ህገመንግስቱን፤ የሚያሻሽሉ፤ አዎጆችን፥ እንጠብቃለን።
ትጥቅ፥ ካነገቡ፥ ሁሉ፥ የሰላም፥ ስምምነት፥ በማድረግ፥ኢሳያስ፥ በኢትዮጵያ፥ ጉዳይ፥ እንዳይፈተፍት፥ በመከልከልና፥ የግብፅን፥ ስውር፥ እጆች፥ በመቁረጥ፥ ኢትዮጵያን፥ ወደ፥ ሰላም፥ አቅጣጫ፥ መውሰድ፥ ይቻላል።