Page 1 of 1

መዓልቱ ዝሓለፎ ስጋ: ምጭናዉ ነይተርፎ!! // ቀናት ያለፈበት ሥጋ ከመሽተት አይድንም!!

Posted: 25 Apr 2023, 17:18
by Wedi
መዓልቱ ዝሓለፎ ስጋ: ምጭናዉ ነይተርፎ!// ቀናት ያለፈበት ሥጋ ከመሽተት አይድንም!!
===
ሃላይ ሰበይትስ: ጸብሓ ይጥዕማ ዝብል ምስላ ኣቦዋት ከም ሎሚ ጌሩ ትርጉም ረኺቡ ኣይፈልጥን። ለባማት ንዓመት ዓመት እንዳሓሰቡ: ዓያሹ ድማ ብዕለት ዕለት እንዳሓሰቡ: ኮታስ ከቢድ እዋን ተሓሊፉ ስገም ንሓምሊ ክዋጥየሉ ምርኣይ ንቡር ኮይኑ ይርከብ።

ኣብ ህሉዉ ፖለቲካዊ ኩነታት ዞባ ቐርኒ ኣፍሪቃ መጺኻ ምዝራብ ኣዝዩ ሕልኽላኽ ዝመልኦ ሙዃኑ ዘረባ ዘድልዮ ኣይኮነን። ገለን ዓቕሚ ስኢኑ: ከም መእሰሪ ዘይብሉ ማእዶ ዘርዚሩ ይስንዱ: ገለን መዓኮሩ ኣሚኑ ከም ሓርማዝ ጉንዲ ይዉሕጥ: ኮታስ ካብ ሱዳን ጀሚርካ ናብ ኢትዮጲያ ኣቲኻ ምስ እትብርብር ግርም'ዩ ዝብለካ።

መሸስ ፖለቲካ ኢትዮጲያ ልክዕ ከምዚ ክልተ ሰኽራማት ቢላርዶ ትጽዉት ኣምስዮም: ብቕርሺ ይበኣሱ'ሞ: ኣብ ኣጋ ምዝዛሞም ብኣረቂ ተዓሪቖም: ኣብራኾም ክሳብ ዝጠልሞም ልፍድድ ሓዲሮም ተደጋጊፎም ዝኸዱ ዓይነት'ዩ። ሰኺሮም ክትብሎም ፈትሊ ገቲሮም ብፈትሊ ዝሓልፉ: ማይ ሰትዮም ክትብሎም ድማ ኣብ ጎልጎል ሜዳ ሸታሕታሕ ኢሎም ምስ መሬት ከዕልሉ: ኣበይ ኣለዉ: ናበይ'ዮም ክኸዱ ፍጹም ክርድኣካ ዘይክእል ሕምብርጅሉ'ዩ ኮይኑ ዘሎ።

መገዲ ሃሰዉ'ንዳበልካ: ጓል መገዲ'ንዳደለኻ!

---
ኣብ ሓደ ዓዲ'ዩ: ክልተ ኣንስቲ ብሓደ ህኩይ ሰብኣይ ተታፋነና'ሞ: ዓዲ ክሳብ ዝኽዕበን ተማናጨታ። ሓንቲአን ድስቲ ክትዉርዉር: ሓንቲኣን ፈርኔሎ ክትዉርዉር: በቃ ዓዲ ህዉከት ኣተዋ። ጎረባብቲ ተሃዊኾም: መሬት ዓይኒ ሕዝ ከተብል ናብ ምዉጣጠን ክኣትዋ ዓዲ ጦቕ ኣቢለን ኣሳጎጎኣ። ዓዲ ዓቕላ ጸንቂቓ ጉዳይ ናብ ባይቶ ክወርድ ኣለዎ ናብ ዝብል ሓሳብ ኣተወት። በዚ መሰረት: ኣንስቲ ተኸሲሰን ኣብ ባይቶ ከም ዝቐርባ ተገብረ።

ዓበይቲ ዓዲ ብሰንኪ'ዘን ክልተ ልኹፋት ኣንስቲ ካብ ጉዳዮም ተሪፎም: ኣብ ትሕቲ ጽላል ዳዕሮ ክእከቡ ተገደዱ። ሰብኣይ ሰበይታ ጭራም ነጸልኣ ሸምጢጣ ናብ ባይቶ ወረደት። ነገር ክጸርየላ ሆጭ በለት። ጭቃ ዓዲ ጉድ ናይ'ዘን ክልተ ኣንስቲ ክሰምዕ ብስቤት ዝተሰኽሰኸ ኣእዛኑ ኩር ኣቢሉ ክጽበ ድሕሪ ምጽናሕ: ከምዚ ክብል ሓሳብ ሃበ-

‘‘መሸስ መንቀኛ ሰብ ጸላኢኡ ይተክል: ፈታዊኡ ድማ ይነቅል እንድዩ: ንስኻትክን ድማ ኣዚኽን ትቃረባ ከም ዝነበርክን'ዩ ዓዲ ዝፈልጥ። እንተኾነ: ብሰንኪ ሓደ ሰብኣይ ኣብ ዕግርግር ኢኽን ጸኒሕክን። ሕጂ ግን ዓዲ ተሃዊኹ: ጉዳይክን መዕለቢ ክንገብረሉ ኢና‘‘ ብምባል: ጉዳየን መዕጸዊ ከም ዝግበረሉ ኣወጀ።

ኣብ መንጎ ዲቕ ዝበለ ክትዕ: ጭቃ ዓዲ ‘‘እሽታ: እሽታ እስከ ዝግ በላ‘‘ ብምባል ኣፈን ኣትሓዘን'ሞ: ነቲ ኣብ ባእሲ ዘእተወን ሃካይ ሰብኣይ ጸዊዑ: ‘‘ንስኻ'ኸ ንመነን ምመረጽካ‘‘ ብምባል ሓተቶ። ወያ ኣብ ማእከል ኣኮታቱ ኮፍ ኢሉ ክሰምዕ ዝጸንሐ ሃካይ ሰብኣ: ‘‘ዋእ- ጭቃ ዓዲ፣ ካብ ቕንፍዝን መፍለስን ምረጹ እንተትበሃሉ'ሲ: ንመነን ምመረጽኩም‘‘ ብምባል ንወዮ ጭቃ ዓዲ ንሕቶ ብሕቶ መለሰሉ። ወዮ ጭቃ ዓዲ ጋን ኣትይዎ: ‘‘እንድዒ‘‘ ብምባል መለሰ። ብመልሲ ጭቃ ዓዲ ዝዓገበ ሃካይ ሰብኣይ ትቕብል ኣቢሉ: ‘‘ክልቲኣተን ወዳእቲ እኽሊ: እንታይ መለሳ ኣለወን‘‘ ብምባል: ዓዲ ብዓዳ: ኣብ ዘይሓዊ ጉዳይ ኮለል ትብል ከም ዘላ ኣርድኣ።

ዓይንና ኣድማ እንዳገበረ እምበር: ንርእዮ ዘሎናስ፥
----

ወያነ-- መንግስቲ ኢትዮጲያ ብጸቕጥታት ሃገራት ምዕራብ ኣጀንዳታቱ ኣብ ሓደጋ ወዲቑ ምስ ምህላዉ: ምስ'ቲ ኣብ ዉሽጡ ሓድነት ምፍጣር ተሸጊሩ ዝርከብ ሰልፊ ብልጽግና ስልታዊ ሓድነት (tactical alliance) ብምምስራት: ናይ ‘‘ጊዜ ምዕዳግን ዕድላት ምምዝማዝን‘‘ ጸወታ ኣብ ምክያድ'ያ እትርከብ። ሰልፊ ብልጽግና ኣብ ክልተ ደንበ ተጎጂሉ ምህላዉ ንመራሕቲ ወያነ ነጺሩ ወጺኡ ኣሎ። ወያነ: ነቲ ሓድነት ክፈጥር ዘይከኣለ'ሞ: ናይ ሕሳብ ምዕሪት ክፈጥር ህርዲግ ክብል ዝጸንሐ ቐ/ሚ ቐሪቡ ክምዝምዞ ምጅማሩ ብዙሕ ክገርመና የብሉን። ኣብ ክልል ኣምሓራ ተበጋጊሱ ዘሎ ዕግርግር'ዉን ንመንግስቲ ኢትዮጲያ ድቃስ ዝህብ ኣይኮነን። ኣብ ዝተናዉሐ: ሕርያታት መንግስቲ ኢትዮጲያ ንቐ/ሚ ከዳኽሞ ከም ዝኽእል ክግመት ይከኣል። ነገሩ: ዕንጸይቲ ፍልጽ ዝጸንሐ ሰብኣይ: ሽሕ ዝኾና ፍላጾ ብሓንቲ ልሕጺ ክጠምረን'ዩ ዝፍትን። ብጥስ እንተኢላ ግን: ብትን ኢለን ናብዛ መሬተን። ደሚርካ ክትርእዮ እንከሎኻ---

ሀ) መንግስቲ ኢትዮጲያ፡ ጭፍራ ማለሊት ሕድገት ተጌሩላ፡ ካብ ገበናታ ናጻ ኮይና ክትነብር፡ ኪኖ ምንባር ሓሊፋ'ዉን ስልጣን ክትማቐል ዝተሰማምዐ ይመስል። እዚ እንታይ ክወልድ'ዩ፡ ኣብ ጊዜ ዘገም ኢልካ ዝምለስ ይኸዉን።

ለ) ጭፍራ ወያነ፡ "ስምምዕ ፕሪቶርያ፡ ኣብ መንጎ ጥሙር ሓይልታትን መንግስታት ኤርትራን ኢትዮጲያን ምጥርጣር (ነቓዕ) ክፈጥር'ዩ" ዝብል እምነት ሒዛ ከም ዝኣተወቶ ንጹር ኮይኑ ኣሎ። ስልታዊ ዝምድናታቶም ብዝግባእ የተግብሩ ኣለዉ ምባል'ዉን ይከእል።

ሐ) ስምምዕ ፕሪቶርያ፡ ኣብ ብዙሓት ሰባት ምጥርጣራት ካብ ምፍጣር ዓዲ ኣይወዓለን። መንግስቲ ኢትዮጲያ፡ በቲ ሒዙዎ ዘሎ ኣካይዳ ክኸይድ ምስ ዝመርጽ፡ ጥንቃቐታት ምግባር ከድልዮ እዩ። እቲ ምንታይ፡ ስድሪ ስጉምቲ፡ ናይ ገዛእ ርእሳ ቱርጓሜ ስለ ዝህልዋ።

ኣብ መደምደምታ-- ኩነታት ኢትዮጲያ ብትኹረት ምክትታል ንግደደሉ እዋን መጺኡ'ዩ። ምስ ኩሉ ዕቃበታቱ፡ እንርእዮን እንሰምዖን ዘሎና ኩነታት: ሰብ ኢልኻ እምኒ ምቑንጣዉ'ዩ ዝመስል ዘሎ። ጥንቃቐታት'ዉን ክሓትት'ዩ።


********************

ቀናት ያለፈበት ሥጋ ከመሽተት አይድንም
==================
ሞኛሞኝ ሴት የራሷ ወጥ ይጣፍጣል ይሉት ተረት እንደዛሬ ሁነኛ ትርጉሙን አግኝቶ አያውቅም ።

ብልሆች ለአመታት ፤ ሞኞች ደግሞ የእለቱን ያስባሉ ።

ከባዱ የጨለማ ጊዜ ሲያልፍ አያ ገብስ ክረምቱን ባሳለፈ ጎመን ላይ ሲመፃደቅበት ማየት ንቡር ሆኖ በገሃድ በኢትይጵያ ሰማይ ስር አይተናል ።

በአሁናዊ የምስራቅ አፍሪካ ላይ ቆሞ መፃኢውን መተንበይ አስቸጋሪ መጠላለፍ የሞላበት መሆኑ ነጋሪ ሳያሻው ፀሐይ የሞቀው እውነት ሆኗል ። አንዳንዱ አቅም አጥቶ ፤ ማሰሪያ እንዳጣ ሰው ፍልጡን መሬት ላይ ዘርግፎ ይሰንዳል ፤ አንዳንዱ ቂጡን ገልቦ እንደ አዞ ይውጣል ፤ አሳህን ከሱዳን ጀምረህ ወደ ኢትዮጵያ ገብተህ ስትፈትሽ እየህነው ያለው ሁሉ ግርም ይላል ።

መቼም የኢትዮጵያ ፖለቲካን ልክ እንደ ሁለቱ ሰካራሞች ነው ፤ ፑል ሲጫወቱ አምሽተው በብር ይጣሉና በአረቄ የሚታረቁ አይነት ነው ፤ እግራቸው እስኪሽመደመድ ሲጋቱ አድረው ተደጋግፈው የሚሄዱ አይነት ነው ፤ ሰክረዋል ስትላቸው ፈትል ገትረው በፈትል የሚራመዱ ፤ ውሃ ጠጥተዋል ሲባሉ ደግም በተቃራኒው ዝርግት ብለው ሜዳ የሚንደባለሉ ፤ የት ናቸው ? ወዴት ነው አቅጣጫቸው ፍፁም የማይገባ ውንግርግር ያለ ሆኗል ነገሩ ሁሉ ።

በመንገዱ ላይ እየተመላለስክ ፤ በመንገዱ ላይ ሂያጅ ሴት ትፈልጋለህ !

አንድ አገር ነው አሉ ሁለት ሴቶች በአንድ ወንድ ተቀናኑና ፤ አገሬው ከቦ በትዝብት እያዬ እየተቧቀሱ ሲናጩ ማየት ይዟል ፤ አንዷ ድስት ስትወረውር አንዷ ፈርኔሎ ( የከሰል ምድጃ ) ትወረውራለች ፤ በአጠቃላይ ከተማው ሁካታ ነገሰበት ፤ ጎረቤቶች ተረበሹ ፤ ለአይን ያዝ ሲያደርግ ወደ ረብሻው እንዳይገቡ የአካባቢው መሰብሰብ ጀመረ ፤ በመጨረሻም አገሬው አቅሉን አሟጦ የነዚህ ረብሸኞች ጉዳይ ለፍርድ መቅረብ አለበት ወደሚል ውሳኔ ገቡ፤ በዚህም መሰረት ሴቶቹ ተከሰው ወደ ችሎት እንዲቀረቡ ተደረገ ።

ታላላቅ የሀገር ሽማግሌዎቹም በነዚህ ሁለት የተለከፉ ሴቶች ከጉዳያቸው እንዲቀሩ ሆነ ፤ ሁሉም ከዋርካ ዛፍ ጥላ ስር እንዲሰበሰቡ ግድ ሆነ ፤ ወንድም ጭራውን ሴቱም ነጠላውን አንጠልጥለው ወደ ችሎት ወረዱ ። የአገሬው ሹም የነዚህ ሴቶች ጉድ ለመስማት በሽበት የተሸፈወነውን ጆሮአቸውን እየኮረኮሩ ሲሰሙ ከቆዩ በኋላ እንዲህ የሚል ሃሳብ ሰጡ - -

"መቼስ ምቀኛ ጠላቱን ይተክላል ፤ ወዳጁን ደግሞ ይነቅላል አይደል የሚባለው ፣ እናንተ ደግሞ በጣም የምትቀራረቡ የልብ ወዳጆች እንደነበራችሁ ነው አገሬው የሚያውቀው ፤ ይሁንና በአንድ ወንድ ምክንያት አንባጓሮ ውስጥ ነው የቆያችሁት ፤ አሁን አገር ስለታወከ ጉዳያችሁን እናያለን

"
በማለት ጉዳያቸው እልባት እንደሚበጅለት አወጁ ።

በዚህ ጫጫታ በበዛበት ሙግት " እሽሽሽ እሽሽሽ እስኪ ዝግ በሉ " በማለት አፋቸው አስያዙአቸውና ፤ ወደ ጠቡ ያስገባቸውን ወንድ ጠሩና

" አንተ እሳ ማንኛዋን በመረጥክ ነበር ?"

በማለት ጠየቁት ። በአጎቶቹ መሀል ተቀምጦ ሙግቱን ሲሰማ የነበረው ወንዱ ሰው

" አይ - ክቡር ሆይ ፤ ከነቀዝ እና ከምስጥ ማንን ይመርጣሉ ቢባሉ ማንን ይመርጡ ነበር "

በማለት ጥያቄው በጥያቄ ለአገሬው ሹም መለሰላቸው ። ሹሙ ጥያቄው ግራ ገባቸው እና እኔ እንጂ ሲሉ መለሱለት ፤ በመልሳቸው የልብ ልብ የተሰማው ወንዱ ሰው " ሁለቱም የእህል ቀበኞች ናቸው ፤ ምን በረከት አላቸው " በማለት ሊድን በማይችል ጉዳይ ላይ መፍትሔ ለማምጣት በከንቱ ሲደክሙ እንደቆዩ ለአገሬው መርዶውን አሰማ ።

--------------------------------------
ዓይናችን አድማ እያደረገ እንጂ የምናየው ነገርስ ....
--------------------------------------
ወያኔ (ትህነግ )--- የኢትዮጵያ መንግስት በምዕራባውን ሃገራት ጫና አጀንዳዎቹ አደጋ ላይ የወደቀ ከመሆኑ አንፃር ፤ ውስጣዊ አንድነቱን ማፅናት የቸገረው ብልፅግና ስልታዊ አንድነት ( Tactical alliance ) በመመስረት

የ" ጊዜ መግዣ ዕድሎችን በማማተር " ጨዋታ በመጫወት ላይ ይገኛል ። የብልፅና ሰልፍ በሁለት ጎራ መከፈሉ ለወያኔ ( ለትህነግ ) መሪዎች ፍንትው ብሎ ተገልጾ ታይቷቸዋል ።

ወያኔ ( ትህነግ ) -

የውስጥ አንድነቱን መፍጠር ያልቻለው ብልፅግና ፤ የሒሳብ ስሌት ሲያጣፋ ወደ ቆየው ጠ/ ሚኒስትር ቀርቦ ሲሸረሽረው መሠንበቱ ብዙም ሊገርመን አይገባም ።

በአማራ ክልል የተሳው ህዝባዊ እንቢተኝነት ለኢትዮጵያ መንግስት እንቅልፍ የሚሰጥ አልሆነም ። በተራዘመ ሂደት የኢትዮጵያ ጠ/ሚንስትሩን ሊያዳክመው እንደሚችል ይገመታል ። ነገርየው እንጨት ሲፈልጥ የዋለ አባወራ ሺህ ፍልጦችን በአንዲት ልጥ ሊያስር እንደሚሞክር ማለት ነው ። ልጧ ብጥስ ያለች ጊዜ ፍልጦቹ ተበትነው ወደ መሬታቸው እንደማለት ነው ።
ደምረን ስናየው....

ሀ ) የኢዮጵያ መንግስት

ለጭፍራ ማሌሌት ( ትህነግ) ይቅርታ ያደረገላት ፤ ከሰራችው ወንጀል ነፃ ሆና እንድትኖር ሲሆን የከበሮ ድለቃው ግን ከነፃነት አልፋ ሥልጣን ለመካፈል የተስማማች ይመስላል ። ይህ ምንን ይወልዳል ? በጊዜ ሂደት በዝግታ የሚመለስ ይሆናል ።

ለ ) ጭፍራ ወያኔ ( ትህነግ ) " የፕሪቶሪያ ስምምነት በጥምር ኃይሉ ፣ በኤርትራ እና በኢትዮጵያ መንግስታት ጥርጣሬ (ስንጥቃት ) ይፈጥራል " የሚል እምነት ይዛ እንደገባችበት ቁልጭ ብሎ በገሃድ ግልፅ ሆኗል ። ስልታዊ ወዳጅነታቸውንም በሚገባ እየተገበሩ ነው ማለትም ይቻላል ።

ሐ ) የፕሪቶሪያ ስምምነት ፤ ብዙዎች በጥርጣሬ አይን የጎሪጥ እያዩት መሆኑ አገር ያወቀው ነው ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በዚህ በያዘው አካሄድ ለመሄድ ከመረጠ ፤ ጥንቃቄ ማድረግም አስፈላጊያችን ነው ፤ ምክንያቱም እያንዳንዷ እርምጃ እራሷን የቻለች ትርጓሜ ስለሚኖራት ።

መደምደሚያ-- የኢትዮጵያን ኩነቶች በአፅንኦት እና በትኩረት መከታተል የምንገደድበት ጊዜ መጥቷል ። በአጠቃላይ ሁኔታው ፡ ለሰው ብለህ በላከው እጅህ ድንጋይ የመዝገን አይነት ነው የሚመስለው ፤ በእርግጥም ጥንቃቄ የሚጠይቅ ነው ።


*******
:!:
Please wait, video is loading...