Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum

Revelations
Senior Member+
Posts: 34573
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: Sudan war: More than 10 Ethiopians killed, embassy ransacked

Post by Revelations » 18 Apr 2023, 08:11

በተጨማሪም በካርቱም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ላይም ጥቃት መድረሱን ገልጿል። የትኞቹ ታጣቂዎች እንደፈጸሙት ባያረጋግጥልንም የኤምባሲዉን ቅጥርግቢ ጥሰዉ በመግባት በግቢዉ በሱዳን የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ባለቤት በሆነበት የመጠለያ ማዕከል ዉስጥ በነበሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ አጸያፊ ተግባራት ጭምር መፈጸማቸዉን ተናግሯል።

የኤምባሲዉ ጥበቃዎች በጦርነቱ ወቅት ከግዳጅ ቦታቸዉ በመነሳታቸዉ የተባለዉ ጥቃት ደርሷል። ታጣቂዎቹም ገንዘብን ጨምሮ ዘረፋ መፈጸማቸዉን ነዉ የተናገረዉ።

በሱዳን ያለዉ ሁኔታ አስከፊ መሆኑን የገለጸልን የመረጃ ምንጭ በዋና ከተማዋ ካርቱም ከፍተኛ ዝርፊ መስፈኑንም ጨምሮ ለብስራት ራዲዮ ተናግሯል። ብስራት ራዲዮ በካርቱም የኢትዮጵያ ኤምባሲን ለማግኘት ሙከራ እያደረገ ነዉ።








Post Reply