በትናንትናው ዕለት የአድዋ ድል በዓልን በማክበር ላይ እንዳለ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በስናይፐር ጥይት ተመቶ ሕይወቱ ያለፈው የሰማዕቱ መምህር መኳንንት ወዳጅ አስከሬን በዛሬው ዕለት የትውልድ ቦታው ጎንደር ራስ ጋይንት ደርሶ በአካባቢው ነዋሪ አቀባበል ተደርጎለታል።
መምህር መኳንንት በአዲስ አበባ ዳግማዊ ምኒልክ መሰናዶ ትምህርት ቤት የፊዚክስ ትምህርት መምህር ነበር።
ወጣቱ መምህር ታሪኩን ስሙን በደማቁ በቀይ ቀለም አጽፎ አልፏል። ከእንግዲህ በየዓመቱ ከጀግኖች አባቶቻችን ጋር አብሮ ይዘከራል።
የወንድማችንን ነፍስ ይማር


