Page 1 of 1
ተመድ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማቅረብ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገው ገለጸ
Posted: 01 Mar 2023, 17:43
by Za-Ilmaknun
While the OPDO gov't is busy training millions of militants for the upcoming confrontations with Ethiopian, UN is sounding that alarm that at least $4 Billion USD is urgently needed to save Ethiopians from the widespread famine and Gov't induced social crisis.
https://www.bbc.com/amharic/articles/c19z2yr4g7do
Re: ተመድ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማቅረብ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገው ገለጸ
Posted: 01 Mar 2023, 17:58
by Za-Ilmaknun
የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት (ኦቻ) በግጭት እና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት እርዳታ ጠባቂ ለሆኑ ኢትዮጵያውን ድጋፍ ለማድረግ ወደ አራት ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል አለ።
ጽህፈት ቤቱ በአውሮፓውያኑ 2022 በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሯዊ አደጋዎች እና በግጭት ምክንያት አስቸኳይ ሰብዓዊ እርዳታ ጠባቂ ሆነዋል ብሏል።
ኦቻ ለዚህ የአውሮፓውያን ዓመት ባወጣው ‘የኢትዮጵያ ሰብዓዊ እርዳታ ዕቅድ’ በመላው አገሪቱ ለሚገኙ ከ20 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ድጋፍ ለማቅረብ 3.99 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
አስቸኳይ ዕርዳታ ከሚያስፈልጋቸው ዜጎች መካከል 4.6 ሚሊዮን የሚሆኑት የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች መሆናቸው ተመላክቷል።
በአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ተጋላጭ ከሆኑ ቀዳሚ አገራት መካከል አንዷ በሆነችው ኢትዮጵያ፣ በአምስት ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች በቂ ዝናብ ባለመጣሉ ከፍተኛ ደርቅ በአንዳንድ የአገሪቱ ክፍሎች መከሰቱን ድርጅቱ አስታውሷል።