የብአደን (አዴፓ) አገራችሁን አድኑ ጩኸት ለማን እና ከነማን ነው?
Posted: 22 Feb 2023, 10:50
የብአደን (አዴፓ) አገራችሁን አድኑ ጩኸት ለማን እና ከነማን ነው? እንደ እኔ የአደፓን ጩኸት ቀለል አድርጌ አላየውም። ይህ ጩኸት ስልጣኔ ሊነካብኝ ነው ከሚል የላቀ ይመስለኛል። ወንበሬ ሊነካብኝ ነው ጉዳይ የሚጣል ባይሆንም ከዚህ ከበድ ያለ የአገሪቱን ህልውና ሊያጠፋ የሚችል ሴራ እንዳለ አሁን የገባቸው ይመስላል። It is a whistle blower of imminent crisis and collapse of the leadership of the country. አንዳንድ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች ይህ ጥሪ ለአማራ ህዝብ የሚመስለውም ይኖራል - እርሱም ትክክል አይደለም። የአማራ ህዝብ ቀደም ብሎ አደፓን ሲጠራው እና ሲፈልገው ነበር። በፊት ሲፈለግ የጠፋ አሁን ፈላጊ ሊሆን እንደት ይችላል? ይህ ጥሪ ከአማራ ውጭ ጭምር ነው። ይህ አገርህ ፈረሰችልህ ኡኡ ታ በድፍን አገሪቱ በኦሮሙማ ለሚሰቃየው ለወላይታ፥ ለጋሞ፥ጉራጌ፥ ጌደዎ ፤ ዳዋሮ ፥(ደቡብ ኢትዮጵያዊያን)፤ ለሱማሌ፥ ለአፋር፥ ለጋማቤላ፤ ለትግሬ፥ ለአማራ፥ ለኦሮሞ እንድሁ ለእስላም ክርስቲያኑ፤ ወዘተ ነው ይሚል አመለካከት አለኝ።
ይህ በብልጽግና መካከል ሰፊ የመሰንጠቅ ምልክት ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ከፍተኛ የኢኮኖሚ፤የሰላም፣ የመረጋጋት እና የፓለቲካ ቀውስጥ ያለች የፈረሰች ( የወደቀ) መንግስት አገር ናት ማለት ነው። አንዳንድ ተንታኞች አብይ አህመድ አስታራቂ በመሆን ስንጥቁን ለመድፈን ይሞክራል - ገድል እንደ ሰራም ይደሰኮርበታል ይላሉ። እኔ ግን እላለሁ ቢጠገንም ሊሆን የሚችል አይደለም - ብዙ እርቀት አያስከድም። የፈራረሰ ጉዳይ ነው። ስለዚህ አገር ወይም ህዝብ ምን ከወድሁ ምን ማድረግ ይጠበቅበታል? ህዝብ የሞራል እና የስነ-ምግባር ልዕልና ሊኖረው ይጠበቃል እንደዚህ ባለ የውደቀት ዘመን። ይህም ማለት ሰው ሁኖ እንደ ሰው ማስብ እና ማድረግ። ከግፍ እና ከብቀላ መራቅ። ጎረቤት ጎረቤቱን ማስዘረፍ እና መዝረፍ ሳይሆም ጎሳ እና ሃይማኖት ሳይለይ የጎረቤቱ ጠባቂ መሆን። የጠፋውን ክቡር ኢትዮጵያዊን ባህል እና ምግባር ፈልጎ ማላማት። እውነተኛውን አቀንቃኝ ከሀሰተኛው መለየት። ህዝብ የለውጥ መሪ እንጅ ተሳፋሪ መሆን የለበትም። ሳያስብ ሳያጤን ሙሴ እያለ የደም ባህር ውስጥ የሚያሰጥምው ሳይሆን እራሱ የለውጡ ባለቤት መሆን አለበት። ለውጥ ይመጣል - አይቀሬ ነው፡ በሞራል እና ስነ ምግባር ግን ዝግጁ መሆን የግድ ይላል። ከመንጋ አስተሳሰብ መፋታት ለመኖር ግደታ መስፈርት ነው።
ይህ በብልጽግና መካከል ሰፊ የመሰንጠቅ ምልክት ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ከፍተኛ የኢኮኖሚ፤የሰላም፣ የመረጋጋት እና የፓለቲካ ቀውስጥ ያለች የፈረሰች ( የወደቀ) መንግስት አገር ናት ማለት ነው። አንዳንድ ተንታኞች አብይ አህመድ አስታራቂ በመሆን ስንጥቁን ለመድፈን ይሞክራል - ገድል እንደ ሰራም ይደሰኮርበታል ይላሉ። እኔ ግን እላለሁ ቢጠገንም ሊሆን የሚችል አይደለም - ብዙ እርቀት አያስከድም። የፈራረሰ ጉዳይ ነው። ስለዚህ አገር ወይም ህዝብ ምን ከወድሁ ምን ማድረግ ይጠበቅበታል? ህዝብ የሞራል እና የስነ-ምግባር ልዕልና ሊኖረው ይጠበቃል እንደዚህ ባለ የውደቀት ዘመን። ይህም ማለት ሰው ሁኖ እንደ ሰው ማስብ እና ማድረግ። ከግፍ እና ከብቀላ መራቅ። ጎረቤት ጎረቤቱን ማስዘረፍ እና መዝረፍ ሳይሆም ጎሳ እና ሃይማኖት ሳይለይ የጎረቤቱ ጠባቂ መሆን። የጠፋውን ክቡር ኢትዮጵያዊን ባህል እና ምግባር ፈልጎ ማላማት። እውነተኛውን አቀንቃኝ ከሀሰተኛው መለየት። ህዝብ የለውጥ መሪ እንጅ ተሳፋሪ መሆን የለበትም። ሳያስብ ሳያጤን ሙሴ እያለ የደም ባህር ውስጥ የሚያሰጥምው ሳይሆን እራሱ የለውጡ ባለቤት መሆን አለበት። ለውጥ ይመጣል - አይቀሬ ነው፡ በሞራል እና ስነ ምግባር ግን ዝግጁ መሆን የግድ ይላል። ከመንጋ አስተሳሰብ መፋታት ለመኖር ግደታ መስፈርት ነው።