የተሸነቆረው መንግስት - ከመሞት መሰንበት?
Posted: 11 Feb 2023, 10:59
በእኔ እይታ የሰሞኑ ቀውስ የሚከተሉትን መሰረታዊ ውድቀቶችንና መነቃቃቶችን ፈጥሯ:
- ዶሮ ጭራ ጭራ መታረጃዋን ታወጣለች እንደሚባለው ሳይከካ የተቦካው የአብይ እንጭጭ መንግስት እራሱን በአደባባይ ሸርፎና ገጥቦ ሽምድምድ ያለ የውዳቂዎች ውዳቂ ሆኗል። ከመሞት መሰንበትን መርጦ ትላንትና የተፋውን መልሶ ቢውጥም፣ ከእንግዲህ በኋላ የተቃዋሚዎችና አኩራፊዎች መፈንጫ ከመሆን አይድንም።
- እንደኔ ሲጠራጠሩና በተስፋ ክር ተንጠልጥለው የነበሩ ሆደ ሰፊና ትዕግስተ-ብዙ ኢትዮዽያኖች ወደ አብይ ጠላትነት ሰተት ብለው እንዲገቡ እራሱ መንግስት በምላሱ መንገዱን ላስ አድርጎ ጠርጎላቸዋል። ዛሬ ቢይንስ ሶስት-አራተኛው የኢትዮዽያ ህዝብ የኦነግ-ሸኔን መንግስት በአጽንዎ ይቃወማል እንዲንኮታኮትም ይመኛል። ከዚህ በተያያዘ የመብት ረገጣን የመቃወሙ ዘመቻ ከየአቅጣጫው ተቀጣጥሎ ይቀጥላል፣ ማንም ሊያቆመው አይችልም። የተሸነቆረ መንግስት ማለት ይኸ ነው። መቀየር እንጂ መጠገን በፍፁም አይቻልም!
- የአናሳው የሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያ አስተዳደር ከሁሉም ክፍለ ሀገራት ተነጥሎ የማፍያ ስብስብና በደምና ብቀላ የሰከረ የሲዖል ምሳሌ መሆኑን እራሱ በግልፅ ለዓለም አሳይቷል። ዛሬ ኦሮሚያ መሄድ ማለት ልክ የመንና ሶማሊያ መሄድ ማለት ነው።
- አድር ባይ የመንግስት ደጋፊዎችና አብሮ አበሮች፣ የቴሌቪዥንና ሬዲዮ አዘጋጆች ከገዳዩ መንግስት ጀርባ በመደበቃቸው እራሳቸውን አዋርደዋል። ከዚህ በኋላ፣ ከኢትዮዽያ ቴሌቪዥን ይልቅ እነ መጋዣው አበበ በለው፣ ቀውሱ ዘመድኩንና አድርባዮቹ ኤርሚያስ ለገሰና ሀብታሙ የተሻለ ተደማጭነት ቢኖራቸው አይደንቀኝም።
- ክፉ ባይኖር የመልካም ዋጋ አይታወቅም እንደሚባለው፣ ሞልቶ የፈሰሰው የህገ-አራዊቱ የኦነግ-ሸኔ ጥጋብ፣ የኢትዮዽያና የዓለም ህዝብ ስለኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታላቅነትና በሳልነት እንዲማር አድርጓል። በአጭር ጊዜ ወደ 70 ሚሊዮን የሚጠጉትን ምዕመናኖቿን ሃይማኖታቸውን እንዲጠብቁ ማነቃቃቷና ማሰባሰቧ፣ እንዲሁም የሌላ ሃይማኖት ተከታዮችና የዓለም ኦርቶዶክስ ማህበርን ከጎኗ እንዲቆሙ ማድረግ መቻሏ ብቃቷንና የፈጣሪን ድንቅ ስራ ፍንትው አድርጋ አሳይታለች። በተቃራኒው አስመሳይ ሀዋርያዎችና ፓስተሮች አንሰው አንሰው ቁጫጭ አክለዋል።
እኔ የማፍረው ትልቁ የኢትዮዽያ አለት ተሰብሯል ሲባሉ ጮክ ብለው “አ ሜ ን” ላሉት ነው።
አውሬው ቆስሏል፣ ግን አሁንም አውሬ ነው!
- ዶሮ ጭራ ጭራ መታረጃዋን ታወጣለች እንደሚባለው ሳይከካ የተቦካው የአብይ እንጭጭ መንግስት እራሱን በአደባባይ ሸርፎና ገጥቦ ሽምድምድ ያለ የውዳቂዎች ውዳቂ ሆኗል። ከመሞት መሰንበትን መርጦ ትላንትና የተፋውን መልሶ ቢውጥም፣ ከእንግዲህ በኋላ የተቃዋሚዎችና አኩራፊዎች መፈንጫ ከመሆን አይድንም።
- እንደኔ ሲጠራጠሩና በተስፋ ክር ተንጠልጥለው የነበሩ ሆደ ሰፊና ትዕግስተ-ብዙ ኢትዮዽያኖች ወደ አብይ ጠላትነት ሰተት ብለው እንዲገቡ እራሱ መንግስት በምላሱ መንገዱን ላስ አድርጎ ጠርጎላቸዋል። ዛሬ ቢይንስ ሶስት-አራተኛው የኢትዮዽያ ህዝብ የኦነግ-ሸኔን መንግስት በአጽንዎ ይቃወማል እንዲንኮታኮትም ይመኛል። ከዚህ በተያያዘ የመብት ረገጣን የመቃወሙ ዘመቻ ከየአቅጣጫው ተቀጣጥሎ ይቀጥላል፣ ማንም ሊያቆመው አይችልም። የተሸነቆረ መንግስት ማለት ይኸ ነው። መቀየር እንጂ መጠገን በፍፁም አይቻልም!
- የአናሳው የሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያ አስተዳደር ከሁሉም ክፍለ ሀገራት ተነጥሎ የማፍያ ስብስብና በደምና ብቀላ የሰከረ የሲዖል ምሳሌ መሆኑን እራሱ በግልፅ ለዓለም አሳይቷል። ዛሬ ኦሮሚያ መሄድ ማለት ልክ የመንና ሶማሊያ መሄድ ማለት ነው።
- አድር ባይ የመንግስት ደጋፊዎችና አብሮ አበሮች፣ የቴሌቪዥንና ሬዲዮ አዘጋጆች ከገዳዩ መንግስት ጀርባ በመደበቃቸው እራሳቸውን አዋርደዋል። ከዚህ በኋላ፣ ከኢትዮዽያ ቴሌቪዥን ይልቅ እነ መጋዣው አበበ በለው፣ ቀውሱ ዘመድኩንና አድርባዮቹ ኤርሚያስ ለገሰና ሀብታሙ የተሻለ ተደማጭነት ቢኖራቸው አይደንቀኝም።
- ክፉ ባይኖር የመልካም ዋጋ አይታወቅም እንደሚባለው፣ ሞልቶ የፈሰሰው የህገ-አራዊቱ የኦነግ-ሸኔ ጥጋብ፣ የኢትዮዽያና የዓለም ህዝብ ስለኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታላቅነትና በሳልነት እንዲማር አድርጓል። በአጭር ጊዜ ወደ 70 ሚሊዮን የሚጠጉትን ምዕመናኖቿን ሃይማኖታቸውን እንዲጠብቁ ማነቃቃቷና ማሰባሰቧ፣ እንዲሁም የሌላ ሃይማኖት ተከታዮችና የዓለም ኦርቶዶክስ ማህበርን ከጎኗ እንዲቆሙ ማድረግ መቻሏ ብቃቷንና የፈጣሪን ድንቅ ስራ ፍንትው አድርጋ አሳይታለች። በተቃራኒው አስመሳይ ሀዋርያዎችና ፓስተሮች አንሰው አንሰው ቁጫጭ አክለዋል።
እኔ የማፍረው ትልቁ የኢትዮዽያ አለት ተሰብሯል ሲባሉ ጮክ ብለው “አ ሜ ን” ላሉት ነው።
አውሬው ቆስሏል፣ ግን አሁንም አውሬ ነው!