Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Meleket
Member+
Posts: 5070
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ሳይመልሱት የሄዱት ጥያቄ . . . ለውጡና . . . ሕዝብ

Post by Meleket » 08 Feb 2023, 10:02

Meleket wrote:
08 Feb 2023, 09:43
ነፍስኄር ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ሳይመልሱት የሄዱት ጥያቂያችን ዳግም ሲነሳ!
Meleket wrote:
23 Jun 2019, 03:26
June 22, 2019 – Konjit Sitotaw
ለውጡና … ሕዝብ
መስፍን ወልደ ማርያም


አንዳንድ ሰዎች ለውጥ የለም ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ስር-ነቀል ለውጥ ተደርጓል ይላሉ፤ ለእኔ ግን ከደርግ የመጀመሪያ ዓመት የሚመሳሰል እንዲያውም ከፍ ያለ ለውጥ አይቼበታለሁ፤ ሆኖም እዚህ አጉል ክርክር ውስጥ አልገባም፤ነገር ግን የተከታተልሁትን ያህል እንደገባኝ እኔ ለውጥ የምለውን ልናገር፤ በዘር ፖሊቲካ የተለያዩ ወንጀሎች እየተለጠፉባቸው ከዕድሜ ልክ እሰከሞት በአሻንጉሊት ዳኞች እያስፈረዱ እስርቤቶቹን ሞልተው እንደነበረ እናውቃለን፤ ዛሬ እነዚህ ሰዎች ሁሉ በነጻ በየቤታቸው ናቸው፤ ይህ ለብዙ ቤተሰቦች ለውጥ ነው፤ ከሁሉም በላይ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት ጋዜጦች፣ ራዲዮኖችና፣ ቴሌቪዥኖች እንደልባቸው እንዲጨፍሩ አድርገዋል፤ ይህም በሚልዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች ለውጥ ነው፤ የፖሊቲካ ቡድኖች ሁሉ እንደልባቸው በነጻነት እየተሰበሰቡ ፐሮግራማቸውን መግለጽና መዘዋወር ችለዋል፤ እንዲውም አንዳንድ የፖሊቲካ ቡድኖች ለውጡ ያመጣውን ነጻነት ወደስድነት ለውጠውት ብዙ ጥፋትን ሠርተዋል፤ ስለዚህ የአገዛዙ ኃይል በለውጡ ምክንያት ሲላላ እኩይ ኃይሎች ይበረታሉ፤ እስከዛሬም ቢሆን እኩይ ኃይሎች እንደተጠናከሩ በመሆናቸው ብዙ ሰዎች መንግሥት መኖሩን ይጠራጠራሉ፡፡

የማስታወስ ችሎታችን ያነሰ በመሆኑና አዲስ ትውልድ በመፍላቱ አናስታውስ ይሆናል እንጂ ደርግ ሥልጣን ሲይዝ ከአንድ ዓመት ያህል በላይ መንግሥት አልነበረም ይባል ነበር፤ ጸሐፌ ትእዛዝ አከሊሉ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከጠቅላይ ሚኒስትርነት በፈቃዳቸው ሲሰናበቱ ወንበሩ ለብዙ ወራት ብዙዎችን እያጓጓ ባዶውን ተቀምጦ ነበር፤ ለጥቂት ወራት በጭንቀት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ቢሮ በተከታታይ የያዙት ልጅ እንዳልካቸው መኮንንና ልጅ ሚካኤል እምሩ ነበሩ፤ጃንሆይ ከዙፋናቸው የወረዱት ጸሐፌ ትእዛዝ አከሊሉ ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ከተሰናበቱ ከዘጠኝ ወራት በኋላ ነው፤ በመሀከሉ የልጅ እንዳልካቸውና የልጅ ሚካኤል ጠቅላይ ሚኒስትርነት እንደነበረ አልረሳሁም፤ ነገር ግን በልጅነት የተቀጩ በመሆናቸውና ፋይዳም ስላልነበራቸው ችላ ብያቸው ነው፡፡

ደርግ ሥልጣን ሲይዝ መንግሥት አልነበረም ቢባልም ሥርዓት አልባነትን የመቆጣጠሪያ ጉልበትና ቁርጠኛነት ነበረው፤ አሁን ግን የተፈለገው ከጉልበት ይልቅ ሕጋዊነት. ከዚያም አልፎ ፍቅር፣ ይቅር ባይነትና ሰላም በመሆኑ ለማኅበረ እኩያን ሁኔታዎችን ያመቻቸ ይመስላል፤ ስለዚህም በኢትዮጵያ ያለው ሥርዓት አልባነት ቢያንስ ለጥቂት ወራት የሚቀጥል ይመስለኛል፤ ይህንን የሥርዓት አልባነት ዘመን ለማሳጠር በሥልጣን ላይ ያሉት ከያዙት የክርስቲያን መንገድ የማይቃረን ዘዴ በቶሎ ቢፈልጉ ከብዙ ጥፋት እንድናለን፡፡

1. ባለሥልጠኖችና ለውጡ

ዛሬ በሥልጣን ላይ ያሉት ሰዎች የኢሕአዴግ አባላት ናቸው፤ ሁለቱም ዓቢይና ለማ የኦሕዴድ አባላት ናቸው፤ እንግዲህ ለውጥ አድራጊዎቹ ሁለቱም የኦሕዴድ አባሎች ናቸው፤ የብአዴን ሰዎች ጎልተው አልታዩም፤ እነዚህ ሁለት የኦሕዴድ ባለሥልጣኖች በአንድ በኩል ራሳቸውን ከአደጋ ለመከላከል በጣም ከባድ ጥረት ያደርጋሉ፤ በሌላ በኩል ለውጡን ወደፊት ለመምራት ይለፋሉ፤

የለውጡ ባለሥልጣኖች በሦስት ኃይሎች ተወጥረዋል። በአንድ በኩል ሥልጣኑን የተቀማውና ያኮረፈው ቡድን ምቹ አጋጣሚ እየጠበቀ ሰላምን ያደፈርሳል፤ በየደረጃው በሥልጣን ላይ ያሉት ደግሞ እንዳይነጠቁ በየፊናቸው እንቅፋቶችን ይፈጥራሉ፤ በተጨማሪ ደግሞ ለውጡ ቀሰስተኛ ሆነብን እያሉ የሚጮሁ አሉ፤ ቆም ብሎ በማሰብ ፖሊሶችን፣ ዓቃብያነ ሕጎችን፣ ዳኞችን በሙሉ አስወጥቶ እንደሀገር መቀጠል እንደማይቻል መገንዘብ አያስቸግርም፤ በሌሎች የተለያዩ ሥራዎችም በወደቁት ባለሥልጠኖች የተሾሙት ሁሉ ስርስሩን መርዝ እየነሰነሱ የሚያደናቅፉ ናቸው፤ ትልቁ የለውጡ መሪዎች ፈተና በጎሠኞች መሀከል የተፈጠረው ፉክክርና ግጭት ነው፡፡

የለውጡ መሪዎች በአላቸው ችሎታ ሁሉ በሰላማዊ መንገድ ሕዝቡን መምራት ይፈልጋሉ፡፡

2. ምሁራንና-ለዉጡ

ምሁራን ማለትን በትክክል ያሳወቀን የለም፤ ስለዚህ እኔ ሆዱ ሰፊ የሆነና ስምንተኛ ክፍል ጨርሶ በፌስቡክ ላይ የሚጽፍ ሁሉ ምሁር ነው ብዬ እነሣለሁ፤ ከዚያ በላይ በአሥራ ሁለተኛ ክፍል በኩልም ይሁን በሌላ በአቋራጭ መንገድ የሚገኙትን የትምህርት መጠሪያ ጌጦች ሁሉ ከነዝባዝንኬያቸው የታቀፉ ሁሉ ምሁራን ናቸው፤ ቄንጠኛ ባርሜጣ ያደረጉና ጥቁር መነጽር የሚያደርጉትንም እጨምራቸዋለሁ፤ የሚሽሎከሎኩም ይኖሩ ይሆናል፡፡

አብዛኛዎቹ ምሁራን ለለውጡ ገለልተኞች አይደሉም፤ እንዲያውም አብዛኛዎቹ ምሁራን ለውጡ የመጣባቸው ናቸው፤ እነዚህ የአንጀራ ምሁራን በእንጀራቸው ለሚመጣ ነገር ዕድሜያቸውም ሆነ ምኞታቸው ለገለልተኛነት አያበቃቸውም፤ በአጠቃላይ ነባር ምሁራን ነባር ሁኔታው የተኙበት ነውና ለውጥን አይደግፉም፤ የእነሱን እንጀራ ለማያወፍር ለውጥ ተቃዋሚ እንጂ ደጋፊ ሊሆኑ አይችሉም፤ በመሠረቱም የእንጀራ ምሁራን ከለውጥ ጋር የሚሰለፉት የተሻለ ወፍራም እንጀራ የሚያቀርብላቸው ሲሆን ብቻ ነው፡፡

አንዳንዶቹ በአማካሪነት፣ በሎሌነት፣ ወይም በአጨብጫቢነት ከመሪዎቹ አጠገብ ለመጠጋት ይፈልጉ ይሆናል፤ አንዳንዶቹ ሥራቸውን፣ ችሎታቸውን በደህና ዋጋ ለመሸጥ ይጥራሉ፤ አንዳንዶቹ ደግሞ መንጠላጠያ ጨብጠው ወደሌላ ዓለም ተምዠግዥጎ ለመብረር ይመኛሉ፤ በአገራቸው ተተክለው የሚቀሩ በጣም ጥቂቶች ናቸው፡፡

ለምሁራን ራሳቸውን ከፍ ለማድረግ የለውጡን መሪዎች ዝቅ አድርጎ መገመት መነሻቸው ይመስለኛል፤ ጥንት በአጼ ዘመን ካሣ ወልደ ማርያም የኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት እንዲሆን ሲሾም እኔ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማኅበር ፕሬዚደንት ነበርሁ፤ በዚህም የተነሣ ለካሣ የምሥራች ደብዳቤ እንጻፍለት ብዬ ሀሳብ አቀረብሁ፤ በዚያን ጊዜ የሰማሁት ተቃውሞ ዛሬ በነዓቢይ ላይ ከሚሰነዘሩት የተለየ አልነበረም፤ ‹‹እኛ የምናውቀውን እነሱ አያውቁም፤ እኛ የምናየውን እነሱ አያዩም፤ እኛ የምንሰማውን እነሱ አይሰሙም፤›› ለድንገተኛ አዲስ ነገር በደመ ነፍስ እንዲህ ዓይነቱን አስተያየት ስንሰጥ እጅግም አያስደንቅም ይሆናል፤ ነገር ግን ሲውል ሲያድር አስተያየታችን ካልተሻሻለ ለውጡን ወደፊት ከመግፋት ይልቅ ወደኋላና ወደጠብ አጫሪነት የሚወስድ ይሆናል፤ የለውጡ መሪዎች ምሁራን ከሚባሉት ያላነሰ እውቀት እንዳላቸው ለመቀበል ትንሽ መመራመርና እውነቱን ማወቅ አስተያየታችንን ያቃናልን ነበር፤ እንዲያውም እንደዓቢይ አህመድ ያለ በብዙ መስኮች በቃሉ የማውረድ ችሎታ ያለው አላውቅም፤ ሊቅ የሚባሉት እንትና እንዲህ አለ፤ እንትና እንዲህ አለ በማለት የሠለጠኑ ናቸው፡፡

3. ሕዝብ

በአጠቃላይ በሕዝቡ በኩል ስለለውጡ ያለው ስሜት እኔ እንደምገምተው በቀል ነው፤ በተለያዩ ሁኔታዎች በድለውናል የሚሏቸውን ባለሥልጣኖች ከሥልጣን ማውረድ ዋናው ፍላጎት ይመስለኛል፤ ይህ ስሜት ወደወጣቶቹ ዘንድ ሲደርስ ኃይልና እልህ ጨምሮ ለግጭት ሊያደርስ ይችላል፤ የማይፈለጉት ባለሥልጣኖች ሁሉ በአንድ ጊዜ ከሥልጣናቸው ቢነሡ የሚከተለውን ትርምስ መገመት አያስቸግርም፡፡

ሕዝቡ እየተረገጠና እየተጠቃ ለዘመናት ይኖራል፤ በደሉንና ቂሙን ድብቅ አርጎ ይዞ ኖሮ የአገዛዝ ለውጥ ሲመጣ የትእግስት ቋቱ ከጫፍ ጫፍ ይተረተራል፤ ፍቅር፣ ውለታና ጉርብትና መቃብር ተቆፍሮላቸው ይገባሉ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቂሙን አይረሳም፤ ቂሙን ደብቆ በምሥጢር ይይዝና ለዘመናት ቆይቶ አጥቂ የነበረው ኃይል ጥቃት ሲደርስበት የኢትዮጵያ ሕዝብ እየፎከረና እልል እያለ በቀሉን ለመወጣት ይጥራል፤ በሰዎች ላይም ሆነ በንብረት ላይ የሚያደርሰው ጥፋት ከፍተኛ ነው፤ በእንደዚህ ያለው ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለበቀልና ለዘረፋ እየፎከረ ይወጣል፤ የሕዝቡ አትኩሮት ባለፈው በደሉና በበቀል ናፍቆቱ ላይ ነው፤ ወደኋላው እንጂ ወደፊት አያይም፤ የወደቀውን አገዛዝ በተሻለ ለውጦ የወደፊት ኑሮውን ለማሻሻል እንዲያስብ መወያየት ያልተለመደ ነው፡፡

ሦስቱም ሃይማኖቶች በነገሡባት አገር፣ ኢትዮጵያ፣ በታሪክ ጸሐፊዎች ሁሉ የክርሰቲያን ደሴት ትባል ነበር፤ ታሪኩን የጠቀስኩት ዓቢይን ለማስገባት ነው፤ ዓቢይ አህመድ በዓቢይ ስሙ ላይ አህመድን ጨምሮ ብቅ ሲል ያልተደነቁት ወሎዬዎች ብቻ ይመስሉኛል፤ ኢትዮጵያ የተደነቀችው ዓቢይ አህመድ ፍቅር፣ ይቅር ባይነት፣ ሰላም … እያለ ብርቅ የሆነበትን ክርስትና መስበክ ሲጀምር ነው! የእናቱ ወሎዬነት አደናቅፎበት አልፎት ይሆናል እንጂ ክርስትና በኢትዮጵያ ከተሰበከ ከሁለት ሺህ አምስት መቶ ዓመታት በላይ ሆኖታል፤ አበሻ ክርስትናን ያሸነፈው በሆዱ ነው፤ አበሻ ለሆዱ ያለውን ፍቅር ዓቢይ መማር ያስፈልገዋል፡፡

ከተለያዩ የውጭ ኃይሎች ጋር የተቃቀፉ ኢትዮጵያውያን ስለኢትዮጵያ የወደፊት ሁኔታ እያጠቆሩና እያመረሩ ያወራሉ፤ ገና ካልደረሰችበት አፋፍ እያንከባለሉ ሊያወርዷትም ይዳክራሉ፤ ሲአይኤ ከሠላሳ ዓመታት በፊት የጠነሰሰውን የኢትዮጵያ ውድቀት ትንበያ ገና አሁን ያነበቡት ምሁሮች ያለማቋረጥ ዛሬ ያነበንቡታል፤ ኢትዮጵያን ትተው ሄደው አሁንም የዳቦ መብያቸው ኢትዮጵያ ነች፤ የፈረንጆችን ዓላማ ለማሳካት ኢትዮጵያን መደፍጠጥ ዳቦ የሚያበላ ሥራ አድርገውታል፤ ለውጡን ለመምራት፣ አቅጣጫውን ለማስለውጥ፣ ፍጥነቱን ለመቀነስ፣ አካሄዱን ለማደናቀፍ የሚጥሩ ክፍሎች በውጭ እርዳታ እንደልባቸው ይንቀሳቀሳሉ፤ ልናውቃቸው ይገባል፡፡

ኢትዮጵያ አጆቿን ወደእግዚአብሔር ትዘረጋለች፤ ይዞ ይደግፋታል!
https://mereja.com/amharic/v2/126560

ይቅርታ ፕሮፌሰር አልገባኝም ትንሽ ሰፋ አድርገው ቢያብራሩት!
ክርስትና በኢትዮጵያ ከተሰበከ ከሁለት ሺህ አምስት መቶ ዓመታት በላይ ሆኖታል፤

ሲሉ ምን ለማለት ነው የተፈለገው። ክርስትና ከክርስቶስ በፊት ነበር እንዴ? ነው ወይስ ክርስቶስ የዛሬ 2500 ዓመት በፊት ነው የነበረው? ግልጽ ቢያደርጉት!

አመሰግናለሁ!

Right
Member
Posts: 4819
Joined: 09 Jan 2022, 13:05

Re: ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ሳይመልሱት የሄዱት ጥያቄ . . . ለውጡና . . . ሕዝብ

Post by Right » 08 Feb 2023, 11:13

That was Prof Mesfin W/m’s opinion.
If he was alive today, he would have written a different opinion on Abiye and Lema. His analysis at the time was wrong. That was then pointed out to him.

Then, he predicted the upcoming northern war accurately

I don’t agree with his definition of the word “intellectual”.

One thing though Ethiopia do not have a well educated intellectuals base in Ethiopia. The best and the brightest if they exist are outside Ethiopia. Harvested by the west or migrated on their own. Just to give you an example, I can’t call myself an intellectual but I am a skilled expert on what I do trained through higher education by Ethiopian tax payers. Because Ethiopia is unliveable I am now benefiting my host country outside of Ethiopia. My brothers and sisters who chose to stay in Ethiopia are preparing their kids for life outside Ethiopia. Some have already made it. This generation of my family will be the last to have lived in Ethiopia. The one who will be born out of Ethiopia will have no meaningful tie with the motherland.I gave you my history but it is the same pattern where eve you go in Ethiopia. Everyone is looking for a way out. Without a properly educated and well trained intellectual pool, in this era, no society will survive.
Maybe be some dark force is behind this to take over Africa, the heaven of earth.


Right
Member
Posts: 4819
Joined: 09 Jan 2022, 13:05

Re: ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ሳይመልሱት የሄዱት ጥያቄ . . . ለውጡና . . . ሕዝብ

Post by Right » 08 Feb 2023, 12:19

No, Professor Mesfin wasn’t always wrong. His contribution to Ethiopia is enormous. He was a teacher, a researcher, author of numerous educative books, founder of the Ethiopian human rights commission etc.
But he has said and done some things wrongly.

Meleket
Member+
Posts: 5070
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ሳይመልሱት የሄዱት ጥያቄ . . . ለውጡና . . . ሕዝብ

Post by Meleket » 17 Feb 2023, 09:41

የፓትርያርኩ የዓቢይ ጾም መልእክት ኣጠቃላዪ ይዘቱ ግሩም ነው!

ነገር ግን እኒህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን መንፈሳዊ ኣባት፡ እንደ ነፍስኄር ብሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም "ከክርስቶስ በፊት ቤተክርስትያናቸውና ሃያማኖታቸው የነበረች ይመስል" :mrgreen: እንዲህ ሲሉ ኣስተውለናቸዋል፡ እኛ ኤርትራውያን የመሃልና የመስመር ዳኞች፡ በኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር። ታዲያ ፓትርያርኩ ትንሽ ኣልተንሸራተቱምን? ኣካፋማ ኣካፋ መባል ኣለበት ዶማም ዶማ!
:mrgreen:
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ፓትርያርክ የአቢይ ጾምን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እነሆ፦ https://mereja.com/amharic/v2/800127

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፤

• በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት እንዲሁም ኢትዮጵውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ!
እንደ ስሑትና ደካማ ሰብአዊ ባሕርያችን ሳይሆን እንደ አባታዊ ቸርነቱ ሁል ጊዜ በምሕረቱ የሚጐበኘን አምላካችን እግዚአብሔር እንኳን ለጾመ ኢየሱስ አደረሰን፤ አደረሳችሁ!
• “ንጹም ጾመ፣ ወናፍቅር ቢጸነ፣ እስመ ከማሁ አዘዘነ፡- ጾምን እንጹም፣ ባልንጀራችንንም እንውደድ፣ እንዲህ አዞናልና” (ቅዱስ ያሬድ)
እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ስንኖር፣ እንድናደርገው ያዘዘን ዓቢይ ነገር ቢኖር ፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ እየመገበ የሚገኘው በፍቅር ነው፡፡ እኛንም ከፍዳ ኃጢአት ያዳነን በፍቅር ነው፡፡ ሕይወታችንና ንብረታችን ተጠብቆ የሚኖረው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡
ግላዊና ማኅበራዊ ኑሮአችን እንዲሁም ሃይማኖታዊ አምልኮአችንና የተግባር እንቅስቃሴአችን በሙሉ ውጤታማ ሊሆን የሚችለው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡
በፍቅር ውስጥ በረከት እንጂ ጉድለት የለም፤ በፍቅር ውስጥ ጤና እንጂ በሽታ የለም፤ በፍቅር ውስጥ ጽድቅ እንጂ ኃጢአት የለም፤ በፍቅር ውስጥ እግዚአብሔር እንጂ ዲያብሎስ የለም፡፡ ይህም በመሆኑ ቅዱስ መጸሐፍ ፍቅርን ‹‹የሁሉም ነገር ማሰሪያ ነች›› በማለት ይገልጻታል፡፡
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከሁሉም የምትበልጠው ታላቋ ትእዛዝ ‹‹ፍቅር›› እንደሆነች ከመግለፁም በላይ ኦሪትና ነቢያት ሁሉ በእሷ እንደሚጠቃለሉ አስተምሮናል፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ፍቅርን እንደ ዓይን ብሌን ስንጠብቃት በእጅጉ የምትጠቅመንን ያህል ጣል ጣል ስናደርጋት ደግሞ በእጅጉ ትጎዳናለች፡፡ በፍቅር እጦት የሚደርሰው ጉዳት በተወሰነ ነገር ብቻ ሳይሆን በነፍስም ሆነ በሥጋ፣ በምድርም ሆነ በሰማይ እጅግ በጣም የገዘፈና የሰፋ ነው፡፡
በሀገራችን የሆነውና እየሆነ ያለውም ይኸው ነው፡፡ ፍቅርን ባጣንባቸው ዓመታት ከየት ወዴት እንደደረስን ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚገነዘበው ነው፡፡ ያተረፍነው ነገርም ምን እንደሆነ የምናውቀው ነው፡፡
ይሁንና የፍቅር እጦት ምን ያህል እንደጎዳን ራሳችን ተገንዝበን ወደ ሰላሙ መንገድ መመለሳችን የተሻለ አማራጭ መሆኑን ሳንመሰክር አናልፍም፡፡ የተጀመረው የፍቅርና የሰላም ጉዞም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ልባዊ ምኞታችንና ጸሎታችን ነው፡፡
ይህንን ሰላም እንዲመጣ ያደረጉ ወገኖችም ሁላቸውን ሳናመሰግን አናልፍም፡፡ ምክንያቱም በሰዎች መካከል ፍቅርንና ሰላምን የሚያደርጉ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉ ብሎ ጌታ እንደ አስተማረን ብፅዕና ይገባቸዋልና ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
የፍጹም ፍቅር መገኛ የሆነው ቅዱስ ወንጌል የሚያስተምረው ፍቅር፣ ራስን ማፍቀር ወይም መውደድ ሳይሆን ራስን መጥላት ባልንጀራን ግን መውደድ ነው፡፡ ወንጌላዊ-ፍቅር ፍጹም ነው የሚያሰኘውም ቅሉ ይህ ነው፡፡
ለሁለት ሺሕ ዘመናት ያህል በቅዱስ ወንጌል አስተምህሮ ላይ የተገነባው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ባህልም ይህን ፍቅር ጠብቆ የሚጓዝ ነው፡፡
ይህም በመሆኑ የኢትዮጵያ አበው መነኮሳት ከነበራቸው ፍቅርና ትሕትና የተነሣ፣ የሹመት ሽሚያ አያውቁም ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር ትልቁን ሥልጣን ይቅርና የአንድ ገዳም መሪ ለመሆንም በእግር ብረት ታስረው በግድ ካልሆነ በቀር እሺ ብለው በፈቃደኝነት ሹመትን አይቀበሉም ነበር፡፡
ራሱን በራሱ መሾም ወይም እኔን ሹሙኝ ብሎ መናገርና የሌላን ድጋፍ መጠየቅ ለኢትዮጵያውያን መነኮሳት ጭራሽ ነውርና ጸያፍም ነበር፡፡
ያም በመሆኑ ነው ከዘመነ ብሉይ ጀምሮ ለሦስት ሺሕ ዘመናት የዘለቀው ሃይማኖታችን ምንም ዓይነት መለያየት ሳያጋጥመው አንድ ሆኖ ሊዘልቅ የቻለው፡፡
ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ጠንካራ አንድነት ለሕዝቡም በመትረፉ የሀገሪቱን አንድነትና ነጻነት አስጠብቆ እስከ ዘመናችን ሊደርስ ችሎአል፡፡ በዚህም ቤተ ክርስቲያናችን የሕዝብንና የሀገርን አንድነትና ነጻነት ለማስጠበቅ ያደረገችውና የምታደርገው ጥረት ሊያስመሰግናት እንጂ ሊያስወቅሳት አይገባም፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ከቅርብ ቀናት ወዲህ በቤተ ክርስቲያናችን ተከሥስቶ የነበረውን ሕጋዊ ያልሆነ ድርጊት የቤተ ክርስቲያናችንን ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና ባሕላዊ መርሕን የናደ፣ እንደዚሁም በኢትዮጵያ ይቅርና በዓለም ታሪክ ተደርጎ የማያውቅ ድርጊት እንደሆነ ቤተ ክርስቲያናችን በአጽንዖት ስትገልጽ ቆይታለች፡፡
ይህንን የቤተ ክርስቲያን ድምፅ በመስማትና በመቀበል ሕዝበ ክርስቲያንና ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለእግዚአብሔር ባቀረቡት ኃዘንና ጸሎት እንደዚሁም ባደረጉት መጠነ ሰፊና ዙርያ መለስ የሆነ የድጋፍ ርብርብ ስሕተቱ ሊታረም ችሏል፡፡
ለተገኘው መንፈሳዊ ውጤትም ክቡር ጠቅላይ ሚንስትርና መንግሥታቸውን፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነትና ሉዓላዊነት እንዲከበር ከፍተኛ መሥዋዕትነት ለከፈለው መላው ሕዝበ ክርስቲያን እንዲሁም ይህ ስሕተት እንዲታረም ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን ተሰልፈው ድምፃቸውን ላሰሙ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በቤተ ክርስቲያናችን ስም ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርብላቸዋለን፡፡
በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ግልፅ ማድረግ የምንፈልገው ከቤተ ክርስቲያናችን ዶግማ፣ ቀኖና እና ሥርዓት መከበር እንደዚሁም ከሉዓላዊ አንድነቷ መጠበቅ በመለስ ያለው ጥያቄ ለማስናገድ ቤተ ክርስቲያናችን ዝግጁ መሆኗን ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያናችን ሕዝቦች በቋንቋቸው የመማር፣ የማስተማርና የማምለክ እንዲሁም የመተዳደር መብትን ካሁን በፊትም፣ አሁንም፣ ካሁን በኋላም የምትነፍግበት መሠረት እንደሌለም ሁሉም ሊያውቀው ይገባል፡፡
ይህም በመሆኑ በቋንቋ የመጠቀም መብት በሕገ ቤተ ክርስቲያናችን ምዕራፍ 2 አንቀጽ 5 ከቁጥር 1-3 ባለው አንቀጽ በሚገባ ተቀምጦ ይገኛል፡፡ ስለሆነም በቋንቋ የመጠቀም ጥያቄ በሕግ ደረጃ ተመልሶ በተግባር እየተሰራበት የሚገኝ መሆኑን ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡
የተወዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፤
ዛሬ ታላቁን ጾማችን በፍቅር ሆነን የምንጾምበት ወቅት ነው፡፡ ሁላችንም እንደምናውቀው ጾም ማለት ስጋዊ ፈቃድን በመግታት ከእግዚአብሔር ጋር ጥብቅ ግንኙነት ለማድረግ የሚካሄድ መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው፡፡
በጌታችን ጾም በተግባር እንዳየነው ጾም ማለት ዲያብሎስ የሚሸነፍበት በአንጻሩ ደግሞ የእግዚአብሔር ሕዝብ አሸናፊዎች የሚሆኑበት ኃይል ነው፡፡
ስለሆነም ጾም የተጋድሎና የሙዓት ሜዳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ የምንታገለውም ልቡሰ ሥጋ ሰውን ሳይሆን ረቂቅ ፍጡር የሆነው ሰይጣን በሰው አድሮ የሚነዛውን አጥፊ ሐሳቡንና ድርጊቱን ነው፡፡
ከዚህም ጋር ሰውነታችን ለዚህ ክፉ መንፈስ ታዛዥ እንዲሆን የሚገፋፉ ጥሉላት መባልዕትን መተው፤ ኃይለ ሥጋን መቈጣጠር፤ ኃይለ መንፈስን ደግሞ ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡ በጾም ወቅት የተራቡትን ማጉረስ የታረዙትን ማልበስ የተበደሉትን መካስ፣ ፍትሕና ርትዕ በማኅበረ ሰብ ውስጥ ማንገሥ ያስፈልጋል፡፡
በጾም ወቅት ኅሊናችን ማሰላሰል ያለበት ሰው ምን አለ? ወይም ምን አደረገ? በሚለው ሳይሆን እግዚአብሔር በፊቱ ምን ዓይነት ሰው እንድንሆንለት ይፈልጋል? በሚለው ላይ ነው፡፡
ስለዚህ ጾማችን በዚህ መንፈስ የተቃኘ ፍቅረ፣ እግዚአብሔርንና ፍቅረ ቢጽን ማእከል ያደረገ፣ መጠራጠርንና አለመተመማንን ያስቀረ፣ የተለያዩትን ያቀራረበ፣ የተሳሳቱትን ያረመ በአንጻሩ ደግሞ ሁላችንን በሰላምና በፍቅር አንድ አድርጎ ያስተሳሰረ ይሆን ዘንድ በዚህ መንፈስ ተነቃቅተን እንድንጾመው አባታዊ ጥሪያችንን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናስተላልፋለን፡፡
በመጨረሻም፤
በሀገራችን እየታየ ያለው የሰላም ጭላንጭልና ችግሮችን በውይይት የመፍታት ዝንባሌ በእጅጉ ጠቃሚና ለሁለንተና ልማታችንና ለዕድገታችን እንደዚሁም ለተሟላ አንድነታችን ጠቃሚነቱ የጎላ ስለሆነ እግዚአብሔር ለዘለቄታው እንዲያሳካልን ከልብ እንድናዝንና ወደ አምላካችን በተመሥጦ እንድንጸልይ በአጽንዖት በማሳሰብ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡
መልካም የጾም ወራት ያድርግልን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር! አሜን
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

DefendTheTruth
Senior Member
Posts: 13243
Joined: 08 Mar 2014, 16:32

Re: ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ሳይመልሱት የሄዱት ጥያቄ . . . ለውጡና . . . ሕዝብ

Post by DefendTheTruth » 17 Feb 2023, 15:15

Right wrote:
08 Feb 2023, 11:13
That was Prof Mesfin W/m’s opinion.
If he was alive today, he would have written a different opinion on Abiye and Lema. His analysis at the time was wrong. That was then pointed out to him.

Then, he predicted the upcoming northern war accurately

I don’t agree with his definition of the word “intellectual”.

One thing though Ethiopia do not have a well educated intellectuals base in Ethiopia. The best and the brightest if they exist are outside Ethiopia. Harvested by the west or migrated on their own. Just to give you an example, I can’t call myself an intellectual but I am a skilled expert on what I do trained through higher education by Ethiopian tax payers. Because Ethiopia is unliveable I am now benefiting my host country outside of Ethiopia. My brothers and sisters who chose to stay in Ethiopia are preparing their kids for life outside Ethiopia. Some have already made it. This generation of my family will be the last to have lived in Ethiopia. The one who will be born out of Ethiopia will have no meaningful tie with the motherland.I gave you my history but it is the same pattern where eve you go in Ethiopia. Everyone is looking for a way out. Without a properly educated and well trained intellectual pool, in this era, no society will survive.
Maybe be some dark force is behind this to take over Africa, the heaven of earth.
unliveable in terms of what?

Is that in terms of money, freedom or something else?

Post Reply