Sudan/Ethiopia border fight started. Abiye was in Sudan recently.
Posted: 03 Feb 2023, 09:10
ሱዳን በኃይል በተቆጣጠረችው የኢትዮጵያ መሬት ጦርነት ተቀሰቀሰ
February 3, 2023
ሱዳን በተቆጣጠረችው የኢትዮጵያ ግዛት ታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ግጭት መቀስቀሱ ከሱዳን በኩል ተስምቷል፡፡ ተቀስቅሷል በተባለው ግጭት የሰው ህይወት መጠፋቱ የተሰማ ሲሆን፣ ግጭቱን የቀሰቀሱት ኢትዮጵያ ታጠቂዎች መሆናቸውን የሚሳይ መረጃ ወጥቷል፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው ሱዳን በኃይል በተቆጣጠረችው አልፋሽጋ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ሲሆን፣ በስፋራው በብዛት የሚገኙ ሱዳናውያን እረኞች የጥቃቱ ሰላባ መሆናቸው ታውቋል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ታጣቂዎች ባለፈው ማክሰኞ በወሰዱት እርምጃ አንድ እረኛ መግደላቸው ነው የተገለጸው፡፡ ዶክተር አብይ አሕመድ ካርቱም ደርሰው ከሱዳን ወታደራዊ መሪዎች ተነጋግረው ከመጡ በሳምንቱ ይህ አይነት ግጭት መነሳቱ አጠያያቂ ነው ።
ጥቃት አድራሾች በእረኞችና በእንስሳት ላይ ማነጣጠራቸው የሱዳንን የእንስሳት ገበያ፣ አገራዊ ምጣኔ ሀብትን እና የእንስሳትን ምርት አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ የሱዳን ፖሊስ አባላት ወደ ቦታው ደርሰው በአካባቢው ጥበቃ እያደረሱ መሆናቸው የተሰማ ሲሆን፤ የሱዳን እረኞችም ወደ ኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ከመጠጋት እንዲቆጠቡ የሱዳን ፖሊስ ማሳሰብ ተጠቁሟል፡፡
የሱዳንና ኢትዮጵያ መንግሥታት በመካከላቸው ያለውን የድንበር ውዝግብ በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸውን መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መቀራረብ የጀመሩት የኢትዮጵያ እና ሰዱን ባለሥልጣናት በኹለቱ አገሮች መካከል ያለውን የድንበርና ሌሎች የኹለትዮሽ ጉዳዮችን በጋራ ለመፍታት ተስማምተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ሱዳን በተቆጣጠረቸው ኢትዮጵያ መሬት ላይ የራሷን ኃይል በማስፈሯ በተደጋጋሚ ግጭት መቀስቀሱ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ በድንበሩ አካባቢ አንድ ጊዜ በሱዳን በኩል አንድ ጊዜ ከኢትዮጵያ በኩል በሚተነኮሱ ጥቃቶች የሰው ሕይወት ይጠፋል፡፡
ኢትዮጵያ እና ሱዳን በድንበር አቅራቢያ ባሉ የጸጥታ ችግሮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ቢስማሙም፣ በታጣቂዎች በተደጋጋሚ የሚከሰቱ ጥቃቶችን ማስቆም አልቻሉም ነው የተባለው፡፡ በሱዳን በኩል ስለተሰማው ጥቃት መፈጸም ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰጠ መረጃ የለም፡፡ ሱዳን 70 ኪሎ ሜትር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት በመዝለቅ በርካታ ቦታዎችን በኃይል ተቆጣጥራ እንደምትገኝ ሲገለጽ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
አዲስ ማለዳ
February 3, 2023
ሱዳን በተቆጣጠረችው የኢትዮጵያ ግዛት ታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ግጭት መቀስቀሱ ከሱዳን በኩል ተስምቷል፡፡ ተቀስቅሷል በተባለው ግጭት የሰው ህይወት መጠፋቱ የተሰማ ሲሆን፣ ግጭቱን የቀሰቀሱት ኢትዮጵያ ታጠቂዎች መሆናቸውን የሚሳይ መረጃ ወጥቷል፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው ሱዳን በኃይል በተቆጣጠረችው አልፋሽጋ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ሲሆን፣ በስፋራው በብዛት የሚገኙ ሱዳናውያን እረኞች የጥቃቱ ሰላባ መሆናቸው ታውቋል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ታጣቂዎች ባለፈው ማክሰኞ በወሰዱት እርምጃ አንድ እረኛ መግደላቸው ነው የተገለጸው፡፡ ዶክተር አብይ አሕመድ ካርቱም ደርሰው ከሱዳን ወታደራዊ መሪዎች ተነጋግረው ከመጡ በሳምንቱ ይህ አይነት ግጭት መነሳቱ አጠያያቂ ነው ።
ጥቃት አድራሾች በእረኞችና በእንስሳት ላይ ማነጣጠራቸው የሱዳንን የእንስሳት ገበያ፣ አገራዊ ምጣኔ ሀብትን እና የእንስሳትን ምርት አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ የሱዳን ፖሊስ አባላት ወደ ቦታው ደርሰው በአካባቢው ጥበቃ እያደረሱ መሆናቸው የተሰማ ሲሆን፤ የሱዳን እረኞችም ወደ ኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ከመጠጋት እንዲቆጠቡ የሱዳን ፖሊስ ማሳሰብ ተጠቁሟል፡፡
የሱዳንና ኢትዮጵያ መንግሥታት በመካከላቸው ያለውን የድንበር ውዝግብ በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸውን መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መቀራረብ የጀመሩት የኢትዮጵያ እና ሰዱን ባለሥልጣናት በኹለቱ አገሮች መካከል ያለውን የድንበርና ሌሎች የኹለትዮሽ ጉዳዮችን በጋራ ለመፍታት ተስማምተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ሱዳን በተቆጣጠረቸው ኢትዮጵያ መሬት ላይ የራሷን ኃይል በማስፈሯ በተደጋጋሚ ግጭት መቀስቀሱ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ በድንበሩ አካባቢ አንድ ጊዜ በሱዳን በኩል አንድ ጊዜ ከኢትዮጵያ በኩል በሚተነኮሱ ጥቃቶች የሰው ሕይወት ይጠፋል፡፡
ኢትዮጵያ እና ሱዳን በድንበር አቅራቢያ ባሉ የጸጥታ ችግሮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ቢስማሙም፣ በታጣቂዎች በተደጋጋሚ የሚከሰቱ ጥቃቶችን ማስቆም አልቻሉም ነው የተባለው፡፡ በሱዳን በኩል ስለተሰማው ጥቃት መፈጸም ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰጠ መረጃ የለም፡፡ ሱዳን 70 ኪሎ ሜትር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት በመዝለቅ በርካታ ቦታዎችን በኃይል ተቆጣጥራ እንደምትገኝ ሲገለጽ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
አዲስ ማለዳ