ኤርትራን መንካ እንደማይታሰብ ኢትዮጵያ አስታወቀች፣ “ውለታን መርሳት ነውር ነው”
Posted: 01 Jan 2023, 11:10

ኤርትራን መንካ እንደማይታሰብ ኢትዮጵያ አስታወቀች፣ “ውለታን መርሳት ነውር ነው”
https://ethio12.com/2023/01/01/2309-164/
JANUARY 1, 2023
በሚል የመንግስት ቁርጥ ያለ አቋም የተገለጸው “ተቃዋሚ” ፓርቲዎችን በመሰብሰብውለታን መርሳት ነውር ነው
በሚል ተደራራቢ ጥያቄ መልስ ሲሰጥ ነው።የኤርትራ ሰራዊት ከትግራይ ለምን አይወጡም
አሉ አቶ ሬድዋን፣በሦስተኛው ዙር አገሪቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለማፍረስ በተካሄደው ጦርነት
ሲሉ ኤርትራን እንደ ጠላት በማየት ጥያቄ ላቀረቡት ምስላዊ ማብራሪያ ሰጡ።የፌዴራል መንግሥት በቆቦ በኩል ባለው ዳገት ወደ ላይ መውጣት ስላዳገተው፣ ትህነግ ያለውን መልክዓ ምድራዊ ጠቀሜታ ተጠቅሞ ቆቦን ተቆጣጥሮ ነበር
ይህ ሲሆን ወቅቱ ክረምት መሆኑ ችግሩን እንዳባባሰው ካስታወሱ በሁዋላ
ሲሉ ኤርትራ ክህደት ተፍጽሞበት የታረደውን የኢትዮጵያ አለኝታ ሰራዊት ተቀብላ ከማስተናገዷ በተጨማሪ ያበረከተችውን የማይረሳ አስተዋጾ ገለጹ።በዝናብ ምክንያት በምዕራብ በኩል ተከዜን የኢትዮጵያ ሰራዊት ማቋረጥ ባለመቻሉ፣ አቅጣጫ ቀይሮ ያለስጋት በዛላምበሳና በአዲግራት በኩል ተከዜን እንዲሻገር የኤርትራ መንግሥት በመፍቀዱ ጦርነቱ ሊቀለበስ ችሏል
ኤርትራ ባትተባበር ኖሮ ምን ሊፈጠር ይችል እንደነበር ሲገልጹ
በማለትለአጭር ጊዜም ቢሆን በራቸውን ባይፈቅዱልን ኖሮ ይኼንን ጦርነት መቀልበስ አይቻልም ነበር፡፡ እንደ አገር ከባድ ፈተና ውስጥ እንወድቅ ነበር
ያሉበትን አንድ ምክንያት ገልጸዋል።ውለታ መርሳት ነውር ነው
ይህንኑ አሳብ በወታደራዊ ቋንቋ ሌተና ጀነራል ባጫ ደበሌ
ማለታቸው ይታወሳል።በቆቦ በኩል ወደፊት የሚገፋ እብድ የለም። ከተፈጥሮ ጋር ውጊያ አይታሰብም። በሌላ አቅጣጫ እናስኬደዋለን
የጠቅላይ ሚንስትር አብይ የደህንነት አማካሪ አቶ ሬድዋን መንግስት ኤርትራ ላይ የያዘውን አቋምና የአቋሙን አግባብነት የሚያሳይ ማብራሪያ ከሰጡ በሁዋላ፣
ሲሉ ወቅሰዋል።የኤርትራ ሠራዊት ከኢትዮጵያ ይውጣ የሚሉት አካላት ለኢትዮጵያ አዝነው አይደለም
ወቀሳቸውን ሲያጠናክሩ
ሲሉ ስለ ብሄራዊ ጥቅምና አገር መውደድ የሚገለባበጠውን የአንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አቋም ለማሳየት ሞክረዋል።ኤርትራ ትውጣ የሚሉ አካላት ሱዳን 50 ኪሎ ሜትር አልፎ ድንበር ወሮ በነበረበት ወቅት አፋቸውን ዘግተው ነበር
ከሃምሳ በላይ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች በተገኙበት ስለ ሰላም አተገባበርና አካሄድ መረጃ ለመስጠት በተካሄደ ውይይት ላይ “ኤርትራ ትውጣ” በሚል ለተነሳው ጥያቄ አቶ ሬድዋን መልሳቸው ከላይ በተገለጸው ምክንያት ብቻ አልቆሙም። ግብጽን አንስተው የትርምስ ገመዱንና እቅዱን በምሳየት
ሲሉ ሞግተዋቸዋል።ይህ ሁሉ ሲሆን የት ነበራችሁ?
ሲሉ ፈትነዋቸዋል።… ግብፅ በሚሊዮን በሚቆጠር ገንዘብ መድባ ለጋምቤላ፣ ለኦነግ ሸኔና ለትህነግ ጭምር በአየርና መሬት ወደ ኢትዮጵያ መሳሪያ እያስገባች ስታስታጥቅ፣ ተቃዋሚዎቹ ፓርቲዎች ምንም አላላችሁም
አክለውም
ሲሉ የሁከቱና የመንግስት መዳከምን መሰረት አድርገው እንደሚንቀሳቀሱ ነግረዋቸዋል።ይህ [የተቃዋሚዎች አቋም] የሚያሳየው እንቅስቃሴው መንግሥትን የሚያዳክም ሲሆን ዝምታ፣ መንግሥትን የሚያግዝ ሲሆን ደግሞ ጩኸት ማብዛት የሚወዱ በመኖራቸው ነው
ሬድዋን
ሲሉ ጠይቀው፣ኤርትራ እኛን አስቸገረን ካላልን ምን አሳሰባቸው?
ሲሉ መንግስትና ኤርትራ ተናበው እንደሚሰሩ፣ ይህ የማይናወጥ አብሮነት እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።ኤርትራ ባስቸገረን ጊዜ እኛ ራሳችን በቃን እንላለን፡፡ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ካሳሰባችሁ ሱዳን ትውጣ ብላችሁ መግለጫ አውጡ
ፍትሃዊ አቋም ማራመድ ሲጀመር
ሲሉ ጉዳዩ ላይ ያለው መነሸዋረር እንዲጠራ አሳስበዋል።ኤርትራ ትውጣ ብትሉ እኛ መረዳት እችላለን
መክረዋል።
ግልጥ ያለውን የመንግስትን አቋም ሲያስታውቁ
ብለዋል።በእኛ [በኢትዮጵያ] አስታኮ የኤርትራ መንግሥትን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም፡፡ ቢያንስ ከተፈጠረው የሰላም ስምምነት አንፃር እኛ እንዳንፈርስ አግዘውናል
ከዚህ ቀደም ትህነግ መንግስትንና ኤርትራን ለማጣላት ሂሳብ እያሰላ የመንቀሳቀስ ስልት እንደሚከተለ ገልጸን መዘገባችን የሚታወስ ነው። የኤርትራ መንግስት ደግሞ
አቶ ሬድዋን ይህንኑ የኤርትራን አቋም ግንዛቤ ውስጥ በመክተት፣ ከዛም በላይ በመናበብ እንደሚሰሩ ግልጽ በማድረግ ዲፕሎማሲያዊ ሃረግ አክለዋል።ትህነግ ስጋት እስከሆነ ድረስ ለደህንነታቸው ሲሉ ከገቡበት ለቀው እንደማይወጡ ሲያስታውቁ መቆየታቸው የሚታወስ ነው።
አሉ የደህንነት አማካሪው፣የጋራ ጠላት የነበረን ቢሆንም
ሲሉ ትህነግ ካልታጠቀ ስጋት እንደማይሆን አስታውቀዋል።ትጥቁን የፈታ የትህነግ ታጣቂ ግን ኢትዮጵያዊ ነው
ትጥቅ መፍታቱ ኤርትራናም ሆነ በትግራይ ዙሪያ ያሉትን ወገኖች ሰላም እንደሚሰጥ ከስምምነቱ በሁዋላ በተደጋጋሚ ሲገለጽ ነበር። በዚሁ ማዕቀፍ ውስጥ ሆነው
ሲሉ አምክንዮ የተሞላው ምላሽ ሰጥተዋል።… ስለዚህ አቅማችን ባለበት እስኪጠናከር ትህነግ መጀመሪያ ትጥቁን መፍታት ይጀምርና እንደማንወጋ ስናረጋግጥ፣ ከጀርባችን ያለው አካል ማንም ይሁን ማን ይውጣልን ማለት እንችላለን
ኢትዮጵያና ኤርትራ የደንነትና ወታደራዊ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።
ወልቃይትን አስመልክቶ ከግራና ቀኝ በተዘዋዋሪ መንገድ ለሚነሳው ጥያቄ ምላሽ እንዲሆን ባስበ መልኩ ይመስላል አቶ ሬድዋን የተናገሩት። ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ የሱዳን መውጪያ በርም ልክ እንደ አሰብ ሁሉ እንዳይወሰድ በሚኡል ስጋታቸውን ጨምረው ላነሱት
ሲሉ ነው አቶ ሬድዋን ያስታወቁት።ከጅምሩ የጦርነቱ ዓላማ ወልቃይትን ማስመለስና ትህነግን ማጥፋት አልነበረም
የጦርነቱ ዋና ዓላማ የአገሪቱን ሉዓላዊነት ማስከበርና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ማስፈን እንደነበር አስታውቀው፣
ሲሉ ትህነግን ማቀፍም ሆነ መግፋት የትግራይ ህዝብ ውሳኔ እንጂ የሌሎች አካላት እንዳልሆነ አመልክተዋል።ትህነግን እንደ ፖለቲካ ኃይል የማጥፋት ዓላማ ያለው ሰው ይኖራል፣ ነገር ግን የፌዴራል መንግሥቱ ዓላማ አይደለም
ከላይ እንደገለጹት ትጥቅ የፈታ ትህነግ ኤትዮጵያዊ ነው።
ወልቃይት በአማራና በትግራይ ክልሎች መካከል ያለ ፀብ በመሆኑ በሁለት ክልሎች መካከል ያለው ፀብ ደግሞ የሚፈታው የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሚመራው ሥርዓት በህግና ህግ ብቻ እንደሆነ አመልክተዋል። የፌደራል መንግስት ባለው የህግ አግባብ የህግ ጨዋታውን ገለልተና ሆኖ ማስፈጸም እንጂ ሌላ ተልዕኮ ሊኖረው እንደማይችል ባለሙያዎችም ሲናገሩ ነበር።
ሲሉ ጉልበት መፍትሄ እንደማያመጣና አንዱ ሲደክም ሌላው ሲበረታ፣ የሚገኝ ድል አስተማማኝ እንደማይሆን ገልጸዋል።የፌዴራል መንግሥትን አቅም ተራ በተራ ጡንቻ እየተፈታተን አንዳችን ሌላችንን ማንበርከክ ይቁም
ሲሉ ያልፈውን አካሄድ ፍትሃዊ እንዳልነበር ያወሱት አቶ ሬድዋን፣ ዛሬ ትህነግ ሸብረክ ሲል ጡንቻ ያለው አካል ይውሰድ ካልን መጪው ትውልድ 20 ዓመት ጠብቆ ድንገት ጡንቻ ካገኘ ዳግም ይወስደዋል።ወልቃይትን ከዚህ ቀደም ትህነግ ጡንቻ ስለነበረው በጉልበት ወስዷል
ሲሉ ጉዳዩ በህግ አግባብ መፍትሄ ሊበጅለት እንደሚገባ ይፋ አድርገዋል።ስለዚህ ዘላቂው መፍትሔ ጡንቻ ሳይሆን ሕግና ሥርዓት ነው
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኤርትራ ወታደሮች ከሽሬና አክሱም ለቀው ድንበር ወደ ራሳቸው ድንበር መጠጋታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። ሮይተርስ ከአቶ ጌታቸው ማረጋግጫ እንዳላገኘ፣ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ተጠይቀው ማረጋገጫም ሆነ ማስተማመኛ እንዳልሰጡት ያስታወቀው፣ ነገር ግን ዕርዳታ ሰራተኞች እንደነገሩት ገልጾ ሮይተርስ ምስክርነቱን ሰጥቷል።
የትህነግ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን ባስረከቡ መጠንና ለማናቸውም የአግወሪቱም ይሁን የጎረቤት መንደሮች ስጋት መሆናቸው በተመናመነ ቁጥር ኤርትራ ወታደሮቿን እንድትስብ ከመንግስት ጋር በስምምነት እንደሚሰራ ግለጸን መዘገባችን ይታወሳል። በዚህ ዜናችን የኤርትራና ኢትዮጵያ ወታደሮች ሰላማታ በመቀያየር ምሽግ መረካከባቸውን ነበር የገለጽነው። አቶ ሬድዋን እንዳሉት
ሲሉ አቶ ሬድዋን ኤርትራ ላይ እጃቸውን ለሚቀስሩ ማሳረጊያ ሰጥተዋል።የእኛ ወገን የምንላቸው የሕወሓት ሰዎች ለ30 ዓመታት ታገልኩለት ያሉትን ሕዝብ ለ30 ዓመታት እየቀለበ፣ እየጠበቀ፣ አብሮ እየሠራና እያረሰ የኖረውን ሠራዊት ከጀርባው አርደው ሜዳ ላይ ሲጥሉት የታደጉት እነዚህ ሰዎች ናቸው፡፡ ለአጭር ጊዜም ቢሆን ውለታን መርሳት ነውር ነው
ከሰላም ስምምነቱ ዜና ደስታና ፈንጠዝያ ጎን ለጎን
የሚሉ ድምጾች የተሰሙትም ለዚሁ ነው።መላከላከያን ያረዱ፣ ያሳረዱና የተባበሩ ላይ ፍትህ ሊበየን ይገባል
ከዚህም በተጨማሪ በትግራይ፣ በአፋርና አማራ እንዲሁም በተዘዋዋሪ በሌሎች አካባቢዎች በንጹሃን ላይ ጭፍጨፋ የፈጸሙና ያስፈጸሙ፣ የህዝብ ንብረትና ማህበራዊ መገልገያዎችን ያወደሙ፣ የጅምላ ግድያ ያስፈጸሙ ወዘተ ላይ ብሄር፣ ሰፈር፣ ቋንቋና ማንነት ሳይለይ ህግ እንዲጸናባቸው ፍትህ ወዳ ዜጎች እየጠየቁ ነው።
ድንገት ወደ መቀለ ባመራው የመንግስት ልዑክ ውስጥ የፍትህ ሚኒስትሩና የእርቅ ኮሚሽን አባላት መካከታታቸው በህግ ተጠያቂነት አግባብ ከትህነግ አመራሮች ጋር ለመነጋገር እንደሆነ ውስጥ አዋቂዎች እየገለጹ ነው።
በዜናው የተጠቀሱት አቶ ሬድዋን ያተናገሩት ከሪፖርተር ቃል በቃለ የተወሰደ ነው።