***********************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰኞ (ታኅሣሥ 24 ቀን 2015 ዓ.ም) ጀምሮ ወደ ሽሬ ከተማ በቀን አንድ በረራ ማድረግ እንደሚጀምር ገለጸ።
አየር መንገዱ ወደ መቐለ የሚያደርገውን መደበኛ በረራ በቀን ወደ ሦስት ከፍ የሚያደርግ መሆኑንም አብስሯል።
በተከታታይም የመንገደኛ ፍላጎት ቁጥርን ከግምት ውስጥ በማስገባት በቀን የሚያደርገውን የበረራ ምልልስ ብዛት እንደሚጨምር ገልጿል።
በመሆኑም ደንበኞቹ ባሉበት ቦታ ሆነው ድረ ገጹን እና የተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያችንን ተጠቅመው ምዝገባ ማድረግ እና ትኬት መቁረጥ የሚችሉ መሆኑን አየር መንገዱ አስታውቋል።
Please wait, video is loading...