ሂደቱን ሳይሆን ምንጩን መታገል ያስፈልጋል
Posted: 21 Dec 2022, 09:13
ሂደቱን ሳይሆን ምንጩን መታገል ያስፈልጋል
አብይ አህመድ ስልጣን ከጨበጠ ጊዜ ጀምሮ በዚች ሀገር የደረሰው ግፍና መከራ ተዘርዝሮ አያልቅም፣፣ ከትህነግ 27 አመት የግፍ ዘመን ያለማጋነን በ100 ወይም በ200 እጥፍ ቢበልጥ እንጅ አያንስም፣፣ የንሮ ውድነቱን ካነሳን ከ200 እስከ 1000 እጥፍ የታየበት ክስተት ነው፣፣ የደህነትን ጉዳይ ካነሳን በጀምላ በየጊዜው ያለማቋረጥ የሚጨፈጨፈው ቢደመር በደርግ እና በትህነግ ዘመን ያለቀውን ህዝብ በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ነው፣፣ ስለ ፍትህ ካነሳን አሁን ስልጣኑን የጨበጡ በጎሳ እና በሙስና የሰከሩትን የሚያገለግል እንጅ ተራውን ህዝብ ያገለለ መረን የለቀቀ የዘረኞች ስርአት ለመሆኑ አሁን እየሆነ ያለው ሁሉንም በአንድ ጎሳ የመጠቅለል ስካር ማስረጃ ነው
ስለዚህም ጎሰኞች እስካሁን እንደታየው የተለያየ አጀንዳ እየሰጡ የህዝቡን ማህበራዊ ህይወት ደህንነት ከድጡ ወደማጡ ( መቀመቁ) ያለማቋረጥ እየከተቱት ይገኛል፣፣ አብይ አህመድ፣ ህዝብን ማንበርከክ እና መግዛት የሚቻለው የህዝብን ከመጠን በላይ ማደህየት ነው ብሎ የሚያስብ ለመሆኑ ብዙ ማስረጃዎች መጥቀስ ይቻላል፣፣ የጎሳ ፖለቲካ ዘርፈ ብዙ አጀንዳዎችን ለመስጠት ይመቻል፣፣ ለተከፋፈለ የፖለቲካ ስርአት ብዙ የሚያጋጭ እና የሚያናውጥ አጀንዳ ለመስጠት ለጎሰኞቹ በጣም ቀላል ነው ፣፣
ስለዚህ መፍትሄው ይህ ሁሉ የማያልቅ አጀንዳ ላይ ጊዜና ጉልበትን ከመጨረስ፣ ከስር መሰረቱ (ምንጩ) ላይ ማተኮር እና መዋጋት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው፣፣ ምንጩን ስንታገል የጎሰኞቹን instrument ወይም ገዢ መሳሪያ ላይ ስናነጣጥር ህዝብ ለጎሰኞች አጀንዳ መስጠት ይጀምራል ማለት ነው፣፣ አጀንዳው ደግሞ የጎሳ ፌደራሊዝምን እና አከላለልን ማፍረስ ይሆናል፣ ስለ ኢትዮጵያ የሚታገል ሁሉ በአንድነት ይህን አጀንዳ ይዞ ከታገለ ጎሰኞችን መቀልበስ የሚቻልበት እድል ከፍ ያለ ይሆናል፣፣ ምክንያቱም ብዙዎች በጎሳ ስርአት የሚተዳደሩ ክልሎች ስርአቱን የግድ ስለማይደግፉት፣፣
አብይ አህመድ ስልጣን ከጨበጠ ጊዜ ጀምሮ በዚች ሀገር የደረሰው ግፍና መከራ ተዘርዝሮ አያልቅም፣፣ ከትህነግ 27 አመት የግፍ ዘመን ያለማጋነን በ100 ወይም በ200 እጥፍ ቢበልጥ እንጅ አያንስም፣፣ የንሮ ውድነቱን ካነሳን ከ200 እስከ 1000 እጥፍ የታየበት ክስተት ነው፣፣ የደህነትን ጉዳይ ካነሳን በጀምላ በየጊዜው ያለማቋረጥ የሚጨፈጨፈው ቢደመር በደርግ እና በትህነግ ዘመን ያለቀውን ህዝብ በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ነው፣፣ ስለ ፍትህ ካነሳን አሁን ስልጣኑን የጨበጡ በጎሳ እና በሙስና የሰከሩትን የሚያገለግል እንጅ ተራውን ህዝብ ያገለለ መረን የለቀቀ የዘረኞች ስርአት ለመሆኑ አሁን እየሆነ ያለው ሁሉንም በአንድ ጎሳ የመጠቅለል ስካር ማስረጃ ነው
ስለዚህም ጎሰኞች እስካሁን እንደታየው የተለያየ አጀንዳ እየሰጡ የህዝቡን ማህበራዊ ህይወት ደህንነት ከድጡ ወደማጡ ( መቀመቁ) ያለማቋረጥ እየከተቱት ይገኛል፣፣ አብይ አህመድ፣ ህዝብን ማንበርከክ እና መግዛት የሚቻለው የህዝብን ከመጠን በላይ ማደህየት ነው ብሎ የሚያስብ ለመሆኑ ብዙ ማስረጃዎች መጥቀስ ይቻላል፣፣ የጎሳ ፖለቲካ ዘርፈ ብዙ አጀንዳዎችን ለመስጠት ይመቻል፣፣ ለተከፋፈለ የፖለቲካ ስርአት ብዙ የሚያጋጭ እና የሚያናውጥ አጀንዳ ለመስጠት ለጎሰኞቹ በጣም ቀላል ነው ፣፣
ስለዚህ መፍትሄው ይህ ሁሉ የማያልቅ አጀንዳ ላይ ጊዜና ጉልበትን ከመጨረስ፣ ከስር መሰረቱ (ምንጩ) ላይ ማተኮር እና መዋጋት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው፣፣ ምንጩን ስንታገል የጎሰኞቹን instrument ወይም ገዢ መሳሪያ ላይ ስናነጣጥር ህዝብ ለጎሰኞች አጀንዳ መስጠት ይጀምራል ማለት ነው፣፣ አጀንዳው ደግሞ የጎሳ ፌደራሊዝምን እና አከላለልን ማፍረስ ይሆናል፣ ስለ ኢትዮጵያ የሚታገል ሁሉ በአንድነት ይህን አጀንዳ ይዞ ከታገለ ጎሰኞችን መቀልበስ የሚቻልበት እድል ከፍ ያለ ይሆናል፣፣ ምክንያቱም ብዙዎች በጎሳ ስርአት የሚተዳደሩ ክልሎች ስርአቱን የግድ ስለማይደግፉት፣፣