ሰለሞን ሹምዬ ከአምስት ሰዓታት እስር በኋላ ተለቀቀ – ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
December 17, 2022
በሃሚድ አወል
ዛሬ ቅዳሜ ረፋድ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋለው ሰለሞን ሹምዬ፤ ከአምስት ሰዓታት እስር በኋላ 10 ሰዓት ከ40 ገደማ መለቀቁን ቤተሰቦቹ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ ። ሰለሞን ዛሬ አምስት ሰዓት ገደማ ላይ በፖሊስ ከተያዘ በኋላ፤ በአዲስ አበባ ገነት ሆቴል አቅራቢያ ወደሚገኘው “የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ መወሰዱን” እህቱ ትግስት ሹምዬ አስታውቃ ነበር።
“ገበያኑ” የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነው ሰለሞን ከእስር ከተፈታ በኋላ ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጋር ባደረገው የስልክ ቆይታ፤ እንዴት እንደተለቀቀ እና በፖሊስ ሲያዝ የነበሩ ሁኔታዎችን በተመለከተ ለቀረቡለት ጥያቄዎች አጭር ምላሽ ሰጥቷል። ሰለሞን ከእስር ስለተለቀቀበት ሁኔታ ሲገልጽ “ምንም የነገሩኝ ነገር የለም። ስንፈልግህ እንጠራሃለን አሉኝ” ሲል ሂደቱን አስረድቷል።
Thread
Ethiopia Insider
@ethiopiainsider
“ገበያኑ” የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነው
ሰለሞን ሹምዬ በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ።ሰለሞን በቁጥጥር ስር
የዋለው ዛሬ ቅዳሜ ታህሳስ 8 ፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ
ቤቱ መሆኑን እህቱ ተናግራለች።