Page 1 of 1
Noble Amara: ክስታኔና ጋፋት፤ የጎጃም አቆልቋይና የክስታኔ እድል!
Posted: 09 Oct 2022, 01:23
by Horus
ደቂቃ 7 ጀምረህ ተከታተል
የሸባል (ሃረሬዎች ሸዋል ይሉታል ። የክስታኔ ጋብቻ (1) በአዳብና ይጀምርና (2) ቸግ፣ (3) ጠፍር፣ (4) እንሾሽላ፣ (5) እረ፣ (6) አገዛን፣ (7) ሸባል፣ (8) እድል፣ (9) አንገት ኧግዳን፣ (10) ቆልፈት የሚባሉ ከ 10 ያላነሱ የድግስና በአል አይንቶች የሚያካትት ታላቅ ካልችር ነው ። አርቲስት ምናሉሽ ረታን እናመሰግናለን !!
Re: Noble Amara: ክስታኔና ጋፋት፤ የጎጃም አቆልቋይና የክስታኔ እድል!
Posted: 09 Oct 2022, 01:55
by Horus
Re: Noble Amara: ክስታኔና ጋፋት፤ የጎጃም አቆልቋይና የክስታኔ እድል!
Posted: 09 Oct 2022, 02:08
by Horus
የፊቃቆ ማይ !
Thank you Minalush!!!
Re: Noble Amara: ክስታኔና ጋፋት፤ የጎጃም አቆልቋይና የክስታኔ እድል!
Posted: 09 Oct 2022, 02:36
by Noble Amhara
Re: Noble Amara: ክስታኔና ጋፋት፤ የጎጃም አቆልቋይና የክስታኔ እድል!
Posted: 09 Oct 2022, 14:28
by Horus
ትክክል ነው ሰርጉ የሸዋ ነው ግን ጭፈራው ያገው ነው። በነገራችን ላይ 'እህም ነው ' የሚባለው የገና አሲናዬ፣ አሲዮ ወዘተ ሁሉ ከአገው የተዋስነው ነው ። ከላይ የጎጃም አቆልቋይ እና እድል ያልኩት ግን አቆልቋይ ምን ማለት እንደ ሆነ አላቅም ። እድል ማለት እድር ማለት ነው ። ስረ ቃሉ መረዳዳት ሲሆን ተራ በተራ መረዳዳት ማለት ነው ። ያ የእድር ትርጉም ። እኔን የገረመኝ ግ ን እስከ ዛሬ የእድል ትክክለኝ ትርጉም እርዳታ ማግኝት ማለት እንደ ሆነ አላቃም ነበር ። ይህ ነው የህዝባችን ጥልቅና ገና የማናውቀው ምስጢር ።
ይህ የሰርግ እድል ባህል የሚነግረኝ አይደለም ለርሻና ለቀብር ለሰርግም መረዳጃ ስርዓት ነበራቸው አይቶቻችን!! ሁሉንም ቆፍረን እናወጣዋለን!!
Re: Noble Amara: ክስታኔና ጋፋት፤ የጎጃም አቆልቋይና የክስታኔ እድል!
Posted: 09 Oct 2022, 14:37
by Noble Amhara
enjoy
Horus wrote: ↑09 Oct 2022, 14:28
ትክክል ነው ሰርጉ የሸዋ ነው ግን ጭፈራው ያገው ነው። በነገራችን ላይ 'እህም ነው ' የሚባለው የገና አሲናዬ፣ አሲዮ ወዘተ ሁሉ ከአገው የተዋስነው ነው ። ከላይ የጎጃም አቆልቋይ እና እድል ያልኩት ግን አቆልቋይ ምን ማለት እንደ ሆነ አላቅም ። እድል ማለት እድር ማለት ነው ። ስረ ቃሉ መረዳዳት ሲሆን ተራ በተራ መረዳዳት ማለት ነው ። ያ የእድር ትርጉም ። እኔን የገረመኝ ግ ን እስከ ዛሬ የእድል ትክክለኝ ትርጉም እርዳታ ማግኝት ማለት እንደ ሆነ አላቃም ነበር ። ይህ ነው የህዝባችን ጥልቅና ገና የማናውቀው ምስጢር ።
ይህ የሰርግ እድል ባህል የሚነግረኝ አይደለም ለርሻና ለቀብር ለሰርግም መረዳጃ ስርዓት ነበራቸው አይቶቻችን!! ሁሉንም ቆፍረን እናወጣዋለን!!
Re: Noble Amara: ክስታኔና ጋፋት፤ የጎጃም አቆልቋይና የክስታኔ እድል!
Posted: 15 Oct 2022, 20:58
by Noble Amhara
Re: Noble Amara: ክስታኔና ጋፋት፤ የጎጃም አቆልቋይና የክስታኔ እድል!
Posted: 15 Oct 2022, 22:42
by Horus
noble amara,
ለዚህ ነውኮ ኤርትራዊያንን የምንወዳቸው ፖለቲካና ባህል ይለያሉ ። በፖለቲካ ከኢትዮጵያ ተለይተዋል ግ ን አቸው ኢትዮጵያ መሆኑን አንድም ቀን ክደው ወይም ኢትዮጵያን ተሳድበው አያውቁም ። ሃይ ሎጋው የሚባለው ካገው ያገኘው ባህል እስከ ደቡብ ኢትዮጵያ ድረስ ነው ሚዘፈነው ። እጅግ የጥንት ባህል መሆን አለበት! ለምሳሌ ላሌ ዬቦ ላሌ (ላለ ዬቦ ላለ) ግዕዝ ሲሆን ጥንት ለአምልኮ የመዘመር ዜማ ነበር ብዬ ነው የደመደምኩት ! ትርጉሙ የበላይ ሁን የበላይ! ታላቅ ሁን! ማለት ነው ። ዛሬ ግ ን የተራ ጉራጌኝ ዘፈን አዝማች ነው ። ትግሬዎች ላሉማዬ ላሎ ይሉታል ! ስለዚህ እንዳንድ እጅግ ጥንታዊ ባህሎች በፍጹም አይጠፉም ። ሊንጉውስቶና አንትሮፖሎጂስቶች የሁለት ህዝቦች የጥንት ዝምድና ለማግኘት የሚጠቀሟቸው የካልቸር ትሬሶች አሻራዎች ናቸው ። ግ ዕዝ ታውቅ እንደ ሆን አላቅም ፤ ቦ ማለት ሆነ፣ ዬቦ ይሁን ማለት ነው ። ላለ፣ ላሌ ላዕላይ የሚለውግ ዕዝ ነው ። በጉራጌኛ ታተ ማለት ታች ማለት ነው ። በግዕዝ ታህታይ የሚለውን ነው እኛ ታተ የምንለው!!! በዚህ መሰረት ነው ላሊ በላ ማለት የበላይ በላይ እንጂ ንብ በላ ማለት አይደለም እያልኩ የምከራከረው ።
Re: Noble Amara: ክስታኔና ጋፋት፤ የጎጃም አቆልቋይና የክስታኔ እድል!
Posted: 16 Oct 2022, 05:11
by Noble Amhara
Hours this song sound very similar to Guraghe