Abiy Ahmed's Ethiopian New Year Gift to Ethiopian People - Petrol Prices are going up by 20% from Tomorrow Morning!
Posted: 28 Sep 2022, 20:10
የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማሻሻያ ተደረገ
******************
የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማሻሻያ መደረጉን የንግድ እና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር ለኢቢሲ በላከው መግለጫ አስታወቀ።
በዚሁ መሠረት ከመስከረም 18 ቀን 2015 ዓ.ም እኩለ ሌሊት 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ የሚከተለው እንዲሆን ተወስኗል።
1. ቤንዚን በሊትር - 57 ብር ከ05 ሣንቲም
2. ነጭ ናፍጣ በሊትር - 59 ብር ከ90 ሣንቲም
3. ኬሮሲን በሊትር - 59 ብር ከ90 ሣንቲም ሲሆን
4. በሥራ ላይ የነበረው ዋጋቸው ባለበት የሚቀጥል የነዳጅ ውጤቶች
4.1. የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር - 76 ብር ከ87 ሣንቲም
4.2. ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር - 43 ብር ከ89 ሣንቲም
4.3. ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር - 43 ብር ከ06 ሣንቲም እንዲሆን ተወስኗል።
******************
የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማሻሻያ መደረጉን የንግድ እና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር ለኢቢሲ በላከው መግለጫ አስታወቀ።
በዚሁ መሠረት ከመስከረም 18 ቀን 2015 ዓ.ም እኩለ ሌሊት 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ የሚከተለው እንዲሆን ተወስኗል።
1. ቤንዚን በሊትር - 57 ብር ከ05 ሣንቲም
2. ነጭ ናፍጣ በሊትር - 59 ብር ከ90 ሣንቲም
3. ኬሮሲን በሊትር - 59 ብር ከ90 ሣንቲም ሲሆን
4. በሥራ ላይ የነበረው ዋጋቸው ባለበት የሚቀጥል የነዳጅ ውጤቶች
4.1. የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር - 76 ብር ከ87 ሣንቲም
4.2. ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር - 43 ብር ከ89 ሣንቲም
4.3. ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር - 43 ብር ከ06 ሣንቲም እንዲሆን ተወስኗል።
Please wait, video is loading...
sarcasm wrote: ↑31 Jan 2022, 20:48ተፅዕኖው የገዘፈው የነዳጅ ዋጋ ማሻሻያ
30 January 2022
አሸናፊ እንዳለ
የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ከዓለም አቀፉ የገበያ ሥርዓት ተነጥሎ በራሱ እንዳይቆም ከሚያስገድዱት አንዱ ነዳጅ ነው፡፡ በማዳበሪያ፣ ድንጋይ ከሰልና ብረት በቅርቡ ራሳችንን እንችላለን ብለው የተነሱት የማዕድን ሚኒስትሩ እንኳን ኢትዮጵያ በነዳጅ ራሷን ትችላለች ለማለት አልደፈሩም፡፡
በዓለም አቀፉ ገበያና በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የነዳጅ ውጤቶች ዋጋ ልዩነት ለማጥበብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በቅርቡ ያፀደቃቸው መመርያዎች ግን ነዳጅ በኢትዮጵያ ሸማቾች ላይ የሚያደርሰው ጫና እየገዘፈ እንደሚሄድ ጠቋሚ ናቸው፡፡
‹‹በሊትር እስከ ሃያ ብር እየደጎምኩ ሳቀርብ ነበር›› ያለው መንግሥት በቅርቡ ግን የአገር ውስጥ ዋጋዎቹን ከዓለም ጋር ለማስተካከል ወስኗል፡፡ በ2013 መንግሥት ወደ 25 ቢሊዮን ብር ድጎማ አድርጌያለሁ ቢልም፣ በኮቪድ-19 ምክንያት ነዳጅ ዋጋ ከበርሜሉ ዋጋ በታች በወረደበት ሰዓት በገፍ ገዝቶ ማከማቸት ግን አልተቻለም፡፡
አዲሱ መመርያ የግሉ ዘርፍ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ሙሉ የነዳጅ ዋጋውን መሸከም እንዲጀምር የሚያዝ ሲሆን፣ ለመንግሥት አገልግሎት ዘርፍ ግን ድጎማው ቀስ በቀስ እየተነሳ በአምስት ዓመታት ውስጥ እንዲያልቅ ወስኗል፡፡
ይኼ ማለት ድጎማው ለግሉ ዘርፍ በየሦስት ወሩ 25 በመቶ እየተነሳ በአንድ ዓመት ያልቃል፡፡ ለመንግሥት ዘርፍ ግን አሥር በመቶ በየስድስት ወሩ እየተነሳ በአምስት ዓመት ያልቃል፡፡
ድጎማው ሲነሳ ለግሉ ዘርፍ ነዳጅ ከዓመት በኋላ በሊትር 50 ብር ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህም አሁን ካለበት 30 ብር አካባቢ በዓመት ውስጥ ከፍተኛ ጭማሪ ይሆናል፡፡
ኢትዮጵያ በዓመት ወደ ሦስት ቢሊዮን ዶላር እያወጣች ወደ አራት ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የነዳጅ ውጤቶችን ታስመጣለች፡፡ ከዚህ ውስጥ ሁለት ሦስተኛው ናፍጣ ሲሆን፣ በብዙ የኢኮኖሚ ዘርፍ ውስጥ ተፈላጊነቱ የጎላ ነው፡፡ የግብርና ሜካናይዜሽን፣ የግንባታ ማሽነሪዎች፣ ጄኔሬተር የሚጠቀሙ ፋብሪካዎችና ፕሮጀክቶች በድጎማው መነሳት ተጎጂ ላለመሆን አዳዲስ የዋጋ ማስተካከያዎችን እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡
የመመርያዎቹ አንዱ ዓላማ በትራንስፖርት ዘርፍ ላይ በኤክሳይስ ታክስ ተሞክሮ ያልተሳካውን የተሽከርካሪዎች ብዛት ለማመጣጠን የታለመ ነው፡፡ መንግሥት ወደ ሕዝብ ትራንስፖርት ሲያደላ ትናንሽ መኪኖች ግን ዋጋቸው ሰማይ ነክቶ እንኳ ከመግዛት የሚቦዝን አልተገኘም፡፡
በአገሪቱ ካሉት ወደ 1.2 ሚሊዮን መኪኖች በሕዝብ ትራንስፖርት ውስጥ የተሰማሩት 300,000 አካባቢ ናቸው፡፡ በእርግጥ ወደ 600,000 መኪና የሚጋፋባት ርዕሰ መዲናዋ 150 ነዳጅ ማደያዎች ብቻ ይዛ የተመጣጠነ የነዳጅ ክፍፍል ማሰብም ሌላው ራስ ምታት ሆኖ የቀጠለ ችግር ነው፡፡
በአሁኑ ሰዓት በዓለም አቀፉ የነዳጅ ገበያ አንድ በርሜል ዋጋ በአጭር ጊዜ ተፈትልኮ ሰማንያ ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ በቅርቡ መቶ ሊገባ እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ሦስት ከመቶ የሚሆነው ቤተሰብ የነዳጅ ውጤቶችን ለማብሰያ የሚጠቀም ሲሆን፣ ከግሉ ዘርፍ ቀጥሎ ተጎጂ እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡
አጥናፉ ገብረ መስቀል (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዋጋ ንረት (Inflation) አስተማሪና ተመራማሪ ‹‹በነዳጅ ድጎማው መነሳት የበለጠ ተጎጂ የሚሆነው ማኅበረሰቡ ነው፡፡ የግሉ ዘርፍ ነዳጅ ቆጣቢ ቴክኖሎጂ መምረጥ ስለሚጀምር ከአካባቢ አንፃር ጥሩ ነው፡፡ ያረጁ መኪኖችን ማስመጣትም ይቆማል፤›› ይላሉ፡፡
‹‹የዋጋ ንረት ከአሁኑ ጣሪያ እየነካ ሲሆን የጦርነቱ ዳፋም አላለቀም፡፡ ከአማራ ክልል የሚመጣ ምርት በሁለት ሦስተኛ ቀንሷል ከሌሎች አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ የሚመጣ ምርትም መቀነሱ ተደማምሮ ኑሮን ከአቅም በላይ ሊያደርግ ይችላል፤›› ሲሉ ያክላሉ፡፡
የነዳጅ አከፋፋዮች ብሶት
Continue reading https://www.ethiopianreporter.com/article/24532