አለም ብሬ
Posted: 13 Aug 2022, 23:04
መንግስት የጉራጌ ክልልነት መብት ለመንሳት የቆጥ የባጡን ሲቧጥጥ አገር አቀፍ የሕገ መንግስት ቀውስ ውስጥ እንደ ሚገባ ማወቅ አለበት ። የጉራጌ ጥያቄ ከዚህ በኋላ ተመልሶ ጠርሙስ ውስጥ አይገባም ። መላ ጉራጌ እንደ ክልል ነው የሚያስበው፣ እንደ ክልል ነው ሁሉን ነገር የሚያየው። ይህ ቡድን ፈለገ አልፈለገ የጉራጌ ጥያቄን አይለውጠውም። ጥቅም አለኝ የሚሉ ጎሳዎች ለጥቅማቸው መታገል ይችላሉ ነገር ግን የጉራጌን ክልልነት መብት ሊገቱ ከቶም አይችሉም። ጉራጌ ወስኗል! የሚወዱን የደግፉናል! የሚጠሉን ይቃውሙናል እንጂ ለውጥ አያመጡም! ጉራጌ በምንም ክለስተር ውስጥ ስለማይገባ ግዜ አታባክኑ!