በሀገራተችን በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ የነበረውና በሞት የተለዬን በድምጻዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ ስም የተቋቋመው ሀጫሉ ፋውንዴሽን ሰኔ 22/2014 ዓ/ም አዋርድ ሊያካሂድለት ነው።
በእዚህ የመጀመሪያው የሀጫሉ አዋርድ መወዳደር የሚችሉት አፋን ኦሮምኛ ዘፋኞች ብቻ ሲሆኑ በሚቀጥለው የሀጫሉ አዋርድ ደግሞ አፍሪካዊን ድምጻዊያኖችን ለማካተት ታቅዷል ብላለች ባለቤቱ ፋንቱ ደምሰው።
አሸናፊዎች የሚለዩት 70% በዳኞች እና 30% በSMS አጭር ቁጥር እንደሆነ ተገልጧል።
የሀጫሉ ሁንዴሳ የምርጫን ሂደት መከታተል የምትፈልጉ በራሱ ስም በተከፈተው ፌስቡክ ፔጅና ዌብሳይት መከታተልና መጠቆም ትችላላችሁ ተብሏል።
Via ዋልተንጉስ ዘሸገር


