የጎሳ ፖለቲካ ሰንዳ
Posted: 08 Jun 2022, 12:50
የዘር ፖለቲካ ሁለት ስለት ያለው ሳንጃ ነው። ሰንዳ ማለት ያ ነው ። የጎሳ ፖለቲካን እንደ ማህበራዊ ሰርዓት ወስደው ተግባራዊ ለማድረግና የኢትዮጵያን አንድ አገርነት፣ አንድ ሕዝብነት ለማፍረስ ድፍን አምሳ አመት የባከኑት የዘር ነጋዴዎች ዛሬ በራሳቸው ሰንዳ እየተቆራረጡ ነው ። ይህ እንደ ሚሆን ሺ ግዜ ነግረናቸው ነበር።
ሰንዳ ለማንም አያዳላም ። ሰንዳ ሌላውን ቆርጦ ሲመለስ ባለቤቱን ይቆርጣል! ሰንዳ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ አማራ አይልም። በጎሳ ሰርዓት ውስጥ ሰዎች በሃይማኖት ተከፋፍለው ይዋጋሉ። በብሄር ተከፋፍለው ይዋጋሉ ። በዘውግ ተከፋፍለው ይዋጋሉ። በክላን፣ በዞን፣ በወረዳ፣ ባውራጃ ተከፋፍለው ይዋጋሉ ።
የኦሮሞች የባንዲራ ንትርክ ሌላ ጥልቅ የሆነ የክርስቲያንና እስላም ኦሮሞ፣ ያሩሲና ወለጋ ኦሮሞ፣ የሸዋና የእንትን ኦሮሞ ማንነት ልዩነት ውጤት ነው ። ኦሮሞ ወደ ስልጣን በወጣና ትግሉ ሁሉ ስለ ሃብትና ሃይል እየሆነ ሲሄድ ክፍፍሉ እየከረረ መሄዱ ሳይንስ ነው ። ይህ ገና መጀመሪያው ነው ።
በነገራችን ላይ አቢይ አህመድም ከዚህ የባንዲራ ትግል ትምህር መውሰድ አለበት ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ወያኔን ያስወገደው በኢትዮጵያ ታሪካዊ ሰንደቅ ስር ተሰልፎ ነው! ከዚህ የሕዝብ ሰንደቅ አላማና ማንነታችን ምልክት እጅህን አንሳ እንለዋለን። ለሱ ለራሱ ጥቅም ስንል! የባንዲራው መዘዝ ብዙ ነው! አይሞትም! አይረሳም!
ሰንዳ ለማንም አያዳላም ። ሰንዳ ሌላውን ቆርጦ ሲመለስ ባለቤቱን ይቆርጣል! ሰንዳ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ አማራ አይልም። በጎሳ ሰርዓት ውስጥ ሰዎች በሃይማኖት ተከፋፍለው ይዋጋሉ። በብሄር ተከፋፍለው ይዋጋሉ ። በዘውግ ተከፋፍለው ይዋጋሉ። በክላን፣ በዞን፣ በወረዳ፣ ባውራጃ ተከፋፍለው ይዋጋሉ ።
የኦሮሞች የባንዲራ ንትርክ ሌላ ጥልቅ የሆነ የክርስቲያንና እስላም ኦሮሞ፣ ያሩሲና ወለጋ ኦሮሞ፣ የሸዋና የእንትን ኦሮሞ ማንነት ልዩነት ውጤት ነው ። ኦሮሞ ወደ ስልጣን በወጣና ትግሉ ሁሉ ስለ ሃብትና ሃይል እየሆነ ሲሄድ ክፍፍሉ እየከረረ መሄዱ ሳይንስ ነው ። ይህ ገና መጀመሪያው ነው ።
በነገራችን ላይ አቢይ አህመድም ከዚህ የባንዲራ ትግል ትምህር መውሰድ አለበት ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ወያኔን ያስወገደው በኢትዮጵያ ታሪካዊ ሰንደቅ ስር ተሰልፎ ነው! ከዚህ የሕዝብ ሰንደቅ አላማና ማንነታችን ምልክት እጅህን አንሳ እንለዋለን። ለሱ ለራሱ ጥቅም ስንል! የባንዲራው መዘዝ ብዙ ነው! አይሞትም! አይረሳም!