********************
(ኢ ፕ ድ)
የምስራቅ አፍሪካ ወታደራዊ መረጃ ተቋማት በጋራ በድንበር፣ በሳይበር፣ በማህበራዊ ሚዲያ ዙርያ፣ በማህበራዊ ጉዳዮች፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በወጣቶችና ሥራ አጥነት በሌሎችም ጉዳዮች ለመሥራት ተስማምተዋል።
አሸባሪዎችንና ፀረ ሠላም ኃይሎችን በጋራ ለመከላከል የሚያስችል ሰነድም ተፈራርመዋል።
በቀጠናው ፀጥታና ደህንነት ጉዳዮች ዙርያ ሲመከሩ የቆዩት የምስራቅ አፍሪካ ወታደራዊ መረጃ ተቋማት ኢትዮጵያ ለፎረሙ መሳካት ላደረገችው አሰተዋጾኦ አመስግነዋል።
የምክክር መድረኩ ከደህንነት ጉዳዮች ባለፈ በዘርፉ የልምድ ልውውጥን ያካተተ ሲሆን የመከላከያ ዋና መሥሪያ ቤትን፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነትን እና የኢትዮጵያ አርተፊሻል ኢንተሊጀንስ ኢንስቲትዩት መስሪያቤቶችን ጎብኝተዋል።
ኢትዮጵያን ጨምሮ ጁቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን፣ ታንዚያና፣ ኡጋንዳ በመድረኩ መሳተፋቸውን ከመከላከያ ሠራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የምስራቅ አፍሪካ የመከላከያ ወታደራዊ መረጃ መድረክ በኢትዮጵያ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን ቀጣዩን የምክክር መድረክ ኡጋንዳ እንደምታዘጋጅ ተጠቁሟል።


Please wait, video is loading...
