Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 23 Mar 2022, 03:23

ልዑላዊቷ ሃገር ሃገረ ዩክሬን፡ "የታላቋ ሩሲያ" ህልምን ለማሳካት በወፈፌው ፑቲን አማካኝነት ስትወረር፡ ጉዳዩ ላዪ ወራሪን ማውገዝ ላይ በማተኮራችን። ድንቁን ኤርትራዊ ድላችንን የሶቭየት ወጠጤ መኮንኖችን ጭምር ልክ ያስገባንበትን የዓፍዓበት ጦርነት የናደው እዝ መደምሰስ 34ኛ ዓመት በዓል ለጥቂት አልፎን ነበር። :mrgreen: ይህን ታሪክ ከዚህ ቀደም እዚህ ዱለነው ነበር viewtopic.php?f=17&t=177312&p=894465&hi ... 9D#p894465 ኣንባቢ መኮምኮም ይችላል። :mrgreen:
Meleket wrote:
07 Mar 2019, 02:14
የሚከተለው ታሪክ “ዝኽርታት ሓመድ ድበ ናደው” ማለትም “የናደው ቀብር ሲዘከር” በሚል ርእስ “ሕድሪ’” የሚባለው አሳታሚ ድርጅት ካዘጋጀው መጸሐፍ የተጨለፈ ታሪክ ነው። ታሪኩ የኤርትራ ህዝብና የነጻነት ታጋይ ልጆቹ ታሪክ ነው። ታሪክ እንዳይሰረቅ ከትውልድ ወደ ትውልድም ይሸጋገር ዘንድ በመጸሐፉ መጀመሪያ ክፍል ያለውን ይዘት እንዳለ ኣቅርበነዋል። ይህን ብርቅ ታሪክ የፈጸሙትም ኤርትራዉያን እንደመሆናቸው መጠን፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች “የኤርትራዉያንን እይታ” ይገነዘቡ ዘንድ ይህን ‘ደርግን’ በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ አኹሪና ብርቕ ታሪክ እዚህ በተወላገደው አማርኛችን እዚህ አቅርበነዋል። መልካም ንባብ!!! በዚያን ግዜ ሕወሓት የኤርትራ ነጻነት ታጋዮችን በማንቋሸሽና በማጥላላት ዘመቻ ተጥዳ ፖለቲካዊ መጨማለቕ ታሳይ ነበር፣ ኤርትራዉያን ታጋዮች ደግሞ ጥበብ በተሞላበት ቅልጣፌን በተካነ ሁኔታ የጥቃት ፕላናቸውን እንዳገባደዱም፣ እንደ ደርጉ ሁሉ ሕወሓትም አራ፣ አፍራና ተደናብራ ነበር ምክንያቱም ይሆናል ብላ ያልጠበቀችው ተአምር ነበርና! ከድሉ ማግስት ግን ወያኔዎች ጅራታቸውን እየቆሎ “እንኳን ደስ አላችሁ! ጀግኖች ወዘተ” የሚል መግለጫ ለማውጣት ተሽቀዳድመው ነበር። ከዚህ ታሪክ እስከ ዛሬ ድረስም ሕወሓት የተማረች አትመስልም፣ በኤርትራ ህዝብና በትግሉ ታዝላ ዝንተዕለት ለመኖር ትሻለች፣ የኤርትራ ህዝብ ግን “በቃ” ብሏታል፣ አሁንም ያለምንም ማንገራገር ከኤርትራ ልዑላዊ ግዛት ብትወጣና ለህግ የበላይነት ብትገዛ አይበጃትም ትላላችሁ?

የናደው እዝ ቀብር ሲዘከር

መግቢያ

“. . . ህዝባዊ ግንባር፡ የናቅፋ ግንባር ድሉን የሚመዝነው፡ በረዢሙ የኤርትራ ህዝብ ትጥቅ ትግል ተጋድሎና በተለይም ባለፉት አስር ኣመታት ውስጥ በታየው ወታደራዊ ክስተቶች ኣዃያ ነው። የሰነዘርነው ጥቃት ኃያል፣ ቅጽበታዊና ትልቅ ጠባሳ ጠላት ላይ እንዳሳረፈ ኣይካድም። ኢትዮጵያዉያን ኤርትራን በኃይል ከያዙበት ግዜ ወዲህ፡ ለመጀመሪያ ግዜ በአእምሯቸው ውስጥ፡ “ለመሆኑ ኢትዮጵያ ኤርትራን ማስተዳደሯን (‘መግዛቷን’) ትቀጥላለች ወይስ ኣትቀጥልም?” የሚል ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽን የሚሻና ፋታ የማይሰጥ ብርቱ ጉዳይ እንዲሆን ያስደረገ ወታደራዊ ጥቃትን ፈጽመን ነው ድልን የተጎናጸፍነው። . . . “ታጋይ ኢሳይያስ አፈወርቅ የህ.ግ.ሓ.ኤ. ዋና ጸሃፊ፡ በሳግም መጽሔት ቁ.14)

በመጋቢት ወር 1988 ናቅፋ ግንባር ላይ መሽጎ የነበረውንና “ናደው እዝ” ተብሎ የሚጠራዉን ግዙፍ የኢትዮጵያ ሰራዊት ክፍል፡ በፍጹም ከበባ ውስጥ በማስገባት የተካሄደ ደምሳሽ ቀለበታዊ ጥቃት፡ በወርቃዊ ድሎች ባሸበረቀውና በተመላው የኤርትራ ህዝብ የተጋድሎ ታሪክ ውስጥ እንደ የአዲስ ምዕራፍ በር ከፋች ሊጠቀስ የሚችል፣ ትልቅ ስትራቴጂያዊ ጥቅም የነበረው ፍጻሜ ነው።
ናደው እዝን የደመሰሰው ወታደራዊ ድላችን በነጻነት ትግላችን ውስጥ ጎልቶ የሚታይ ይሁን እንጂ፡ የህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ ሰራዊት፡ ወደዚህ ግዙፍ ስትራቴጂያዊ የማጥቃት እርምጃ ለመሸጋገር፡ አስቀድሞ ያሳለፋቸው ፋታ የማይሰጡ ተደጋጋሚ ውጊያዎች፡ እጅግ ረዢም ትዕግስትና ብርቱ ጽናት የሚጠይቁ ነበሩ። ስለሆነም የናደው እዝ መደምሰስ፡ አስቀድሞ ለአስር አመታት በቋሚ ሰንሰለታዊ ምሽጎች ናቕፋ ሰሜናዊ ምስራቕ ሳሕልና ባርካ ላይ የተካሄዱት ብርቱ ውጊያዎች ፍሬ ወይ ምርት ነው። በተጨማሪም በጠላት ወረዳ ውስጥ በደፈጣ ውጊያ በፈንጅ ቀበራና በመሳሰሉት የተቀነባበሩ እረፍት የማይሰጡ ውጊያዎች ታግዞ፡ የኢትዮጵያ ሰራዊትና አጋሮቹ መቆሚያና መቀመጫ እስኪያጡ ድረስ የተካሄዱ ተደጋጋሚ ውጊያዎች ፍሬ ነው።

አጭር ቅድመ ታሪክ

በ1977-1978 አምስት ተከበው ከቀሩ ከተሞች በስተቀር፡ መላው ኤርትራ በኤርትራዉያን ታጋዮች ቁጥጥር ስር ሆኖ ነበር። የደርግ ስርዓት ኤርትራዉያን ታጋዮች በሚሰነዝሩበት ጥቃት ብቻ ሳይሆን፡ ከሶማሊያ ጋር ያካሂደው በነበረ ውጊያ ወተሃደራዊ ኣቅሙ እጅግ ተዳክሞ ነበር። የኤርትራ ህዝብ ከዛሬ ነገ ነጻነቴን እጎናጸፋለው ይል በነበረበት ወቅት ግን፡ በወታደራዊ የኃይል አሰላለፍ ሚዛን የሚያዛባ መሰረታዊ ለውጥ ያስከተለ የልዕለኃያሏ ሃገር የሶብየት ህብረት እጅ ቀጠናችን ውስጥ ገባ። ደርግም የሶቭየት ህብረትን ግዙፍ ድጋፍ ኣግኝቶ፣ ባጭር ጊዜ 300,000 ዘመናዊ መሳርያ የታጠቀ፡ በጥቁር አፍሪካ ውስጥ እጅግ ብርቱውን ወታደራዊ ኃይል አንጾ፣ ከመቅጽበት ከተከላካይነት ወደ አጥቂነት ተሸጋገረ።

በ1978 አጋማሽ፡ ደርግ በሶማሊያ ሃይሎች ላይ እጅግ ግዙፍ ጥቃት ከፈተ። በሳምንት ውስጥም የሶማሊያን ጦርነት በድል አገባዶ፡ “የምስራቅ ድል በሰሜን ይደገማል!” በሚል መፈክር ታጅቦ፡ ወደ ሰሜን በማቅናት የኤርትራን ህዝብ ትግል “ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ” ብሎ በሰየመው ጥቃት ለመደምሰስ እጅግ ግዙፍ ወረራን ጀመረ። ጦርነቱ “በጉንዳንና በዝሆን” መካከል እንደሚደረግ ኣይነት ግጥሚያ ነበር። ስለሆነም ህዝባዊ ግንባር አቅሙንና ብቃቱን ገምግሞ ይህን እጅግ ግዙፍ የሆነ ወራሪ ሰራዊት በተራዘመ ውጊያ ለማዳከም፡ ነጻ አውጥቷቸው ከነበሩ ቦታዎች ደረጃ በደረጃ እያፈገፈገ፡ የጠላትን ኃይል በአመቸው ቦታና ግዜ እየገጠመ፡ ስትራቴጂያዊ ማፈግፈግ ለማድረግ ወሰነ። በዚህ መሰረትም፡
በመጀመርያው ወረራ፡ ህ.ግ. ከደቡባዊና ምስራቃዊ ኤርትራ ሲያፈገፍግ
በሁለተኛው ወረራ ከሰሜናዊ ግንባር አፈገፈገ
በሶስተኛው ወረራም፡ ከከረንና አፍዓበት አካባቢ በማፈግፈግ ቋሚ ምሽጉ ይሆን ዘንድ ወደ መረጠው የናቅፋ ተራራዎችና ሰሜናዊ ምስራቅ ሳሕል አቀና። (የህዝባዊ ሰራዊት ስትራቴጅ ቀድሞም ቢሆን እያፈገፈግክ በሚመችህ ቦታ ጠላትን ድባቅ መምታት መሆኑ የሚያውቅ ነው ሚያውቀው።)

የህዝባዊ ግንባር ሰራዊት በተመቸው ስፍራ ሁሉ ብርቱ ተቃውሞ እያደረገ እያጓራ በመጣበት ጠላት ላይ ከባድ ኪሳራን እያከናነበ በየካቲት 1979 ናቅፋ አካባቢ ደረሰ። በናቅፋ መግቢያ በርም በግራና ቀኝ “እምባ ደንደን” በተባለ ተራራ ላይ መሸገ። ይህ ስፍራ የመጨረሻ የመከላከያ መስመር ይሆን ዘንድ አስቀድሞ በጥናት የመረጠው ቦታ ነበር። ሆኖም የናቅፋ ግንባር ልክ በዚህ ሁኔታና ግዜ ነበር የተመሰረተው። መጀመሪያ ላይ የግንባሩ ስፋት እጅግ ውሱንና ጠባብ ነበር። የጠላት ሰራዊት በተወሰነ ቦታ ጥሶ ወይ በስቶ ለማለፍ የሚያደርጋቸው ተከታታይና ተደጋጋሚ ጥቃቶች ውጤት አልባ ሲሆኑበት ግዜ፡ በቀጣይ ወረራዎቹ ማለትም (በ4ኛ 5ኛና 6ኛ) ወረራዎቹ ወቅት፡ ሆን ብሎ የወገንን ኃይል ሚዛን ለማሳሳትና ለማራራቅ፡ በግንባሩ ሁለት ክንፎች የሰራዊቱን ይዞታ እየለጠጠ ሰፊ ቦታ ለመሸፈን ብርቱ ጥረት አካሄደ። ከናቅፋ ግንባር በተጨማሪም የሰሜናዊ ምስራቅ ሳህል ግንባርና የሓልሓል ግንባርም በተመሳሳይ መልኩ ይዞታቸው እየሰፋ በመሄዱ በመጨረሻ ሶስቱም ግንባሮች እርስ በርስ ተሳስረው ነበር ለማለት የሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተደረሰ። በዚህም ለአስር ዓመታት ያህል ያለማቋረጥ በተደረገ ብርቱ የምከታ ውጊያ፡ ሁለቱም ተጻራሪ ወገኖች ምሽጋቸውን የማደላደል ስራ በቀጣይነት ይተገብሩ ስለነበር፡ በሁለቱም ወገኖች መካከል በፈንጅ የታጠረ የ667 ኪሎሜትር ርዝመት ያለው ብርቱ ምሽግ ተፈጥሮ ነበር። (የኤርትራ ህዝብ የሕወሓትን አካሄድና የድንበር ብይንን አፈታት በተመለከተም ተመሳሳይ ስትራቴጂ የተከተለ ይመስላል፡ ከብርቱ የእልህ ምከታ በኋላ ድንበሩን የሚያስከብርበትና ልዑላዊ ግዛቱን በጠቅላላ ያለአንዳች መሸራረፍ የሚያስተዳድርበት መድረክ ላይ ከትናንት ይልቅ ዛሬ ይበልጥ ተቃርቧል ለማለት ይቻላል።)

ከ1978 አጋማሽ እስከ 1988 ለአስር ዓመታት የቀጠለ ብርቱ የመረባረብ ውጊያ ከተካሄደ በኋላ፡ ያ ልዕለ ኃያል በሆነችው የሶቭየት ህብረት እጅግ ግዙፍ በሆነ ወታደራዊ፣ ገንዘባዊና ቴክኒካዊ ምክር እየተለገሰለት፡ የኤርትራን ህዝብ ትግል ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ ለመደምሰስ የተነሳው ወራሪ የኢትዮጵይ ሰራዊት፡ ከባድ ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳቱን ተሸክሞ፡ ከማጥቃት ወደ መከላከል ስትራቴጂውን እንዲቀይር ተገዷል። ውጊያም ያለ እረፍት በመቀጠሉና ስለተራዘመበትም፡ የኢትዮጵያ ሰራዊት መጨረሻ ላይ ተስፋ እየቆረጠ፣ የመዋጋት ወኔው እየጠፋበት ሞራሉ እየላሸቀ ሂዷል።

እጅግ ረቂቅና ውስብስብ የስለላ ጥናት በማድረግ፡ የጠላት ሁኔታ፡ ከዕለት ወደ ዕለት በትክክል ይገመግም የነበረው የህዝባዊ ግንባር አመራርም፡ በ1987 የጠላትን ቀልብ ከቅድመ ግንባር ወደ መሃል ወይም የጠላት ይዞታ ውስጥ የሳበ፡ ተከታታይ የደፈጣና አጥቅቶ የመሰወር ተልዕኾዎችን ሆን ብሎ ተያያዘው። በግንባር ላይ የነበረውን የጠላት ሁኔታ ለመፈተሽም በታሕሳስ ወር 1987 በናቅፋ ግንባር መካከለኛ መስመር ላይ፡ በተወሰኑ አካባቢዎች መጠኑ አንስተኛ የሆነን ጥቃት በማካሄድ፡ ጠላትን በመግፋት ናደው እዝን ለመደምሰስ ለቀጣዩ ብርቱ የማጥቃት እርምጃ መረማመጃ የሚሆነውን ስትራቴጂያዊ ቦታዎችን በቁጥጥሩ ስር አዋለ።
በነዚህ ብርቱ ጥቃቶች የደነገጠው የደርግ ስርዓት መሪ መንግስቱ ሃይለማርያምም፡ በየካቲት 1988 ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ በመምጣት፡ መላ ኤርትራ ውስጥ የነበረውን የሁለተኛ አብዮታዊ ሰራዊት ብሎ የሚጠራዉን ሰራዊት አመራሮች ጋር ስብሰባ ካካሄደ በኋላ፡ ናደው እዝ እንዲዳከም ምክንያት የሆኑት እንዲሁም በወርሓ ታሕሳስ ግንባር ናቅፋ ላይ ላጋጠመው ሽንፈት ዋንኛ ተጠያቂ ነው ያለውን፣ የግንባሩን ኣዛዥ ብሪጋዴር ጀነራል ታሪኩ ያይኔ መሆኑን በመግለጽ፡ ከሰራዊት ፊት እንዲረሸን አደረገ። በደጋማው የኤርትራ ክፍል በደፈጣ ውጊያ በደርግ ሰራዊት ላይ ለደረሰው ኪሳራም የመክት እዝን ሃላፊ ብሪጋዴር ጀነራል ከበደ ጋሼን ተጠያቂ መሆኑን ኋላፊነት በማሸከም፡ ከሰራዊቱ ፊት ማእረጉን በመግፈፍ ያለ ጥሮታ እንዲባረር አደረገ። የሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ማለትም የ‘ሁ.አ.ሰ.’ አዛዥ የነበሩት ሜጀር ረጋሳ ጂማንና ምክትሉን ሸዋረጋ ቢሆነኝን ከሌሎች ከ20 በላይ የሚሆኑ ከፍተኛ የሰራዊት አዛዦችንም፡ ከኤርትራ ወደ የኢትዮጵያ ሌላ ክፍል ቀየራቸው።

በዚያን ወቅት መንግስቱ ሃይለማርያም የወሰደው የተስፋ መቁረጥ እርምጃ የሰራዊቱን ድክመት እንደገና አባብሶት ነበር። የደርግ ስርዓት፡ ከዚህ ሌላ፡ በኤርትራ ደጋማ ክፍሎች በተከታታይ ይደርስበት የነበረውን ብርቱ የደፈጣ ውጊያ ሊቋቋም ባለመቻሉ፡ ይህን ውስጣዊ መስመሩን ወይም ውስጣዊ ይዞታውን ለማደላደል ከዋና የግንባር ክፍሎች ቀስ በቀስ ሃይሉን እያመጣ በውስጣዊ ይዞታው እንዲያሰፍር ይገደድ ነበር።
ይህን ወታደራዊ ሁኔታ በትኩረት ይከታተል የነበረው የህዝባዊ ግንባር አመራርም፡ ‘ናደው እዝ’ን ለመደምሰስ አስቀድሞ ያካሂደው የነበረውን ጥናትና ይመረምረው የነበረን የማጥቃት ውጥን ተግባር ላይ የሚያውልበት የዜሮ ሰዓት እንደተቃረበ ገመገመ። የናደው እዝን የመደምሰስ ተልእኮ ከመከናወኑ በፊት ማለትም ከየካቲት 25-28 1988 የተካሄደው ሁለተኛው የህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ ማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባም ይህን የሚያመላክት አንድምታ ነበረው።

“ማእከላዊው ኮሚቴ . . . . ወታደራዊ ጥቃቶችን ይበልጡኑ ማበረታታትና ይዞታውንም ማስፋት የሚያስችል፡ ጠላትም ዓቅሙን እንዲያሻሽል ፋታ የማይሰጥ ወታደራዊ የስራ መደብንና ፕላንን አዘጋጅቷል።” ይላል ያኔ የወጣው የአቋም መግለጫ።

ይህን ዓላማ ለማሳካት የተመደበው የመጀመሪያ ውጥን፡ ናደው እዝን በመክበብ መደምሰስ ነበር። የህዝባዊ ግንባር አመራር ክፍል ይህን ዓይነት ትልቅና ደፋር እርምጃን ለመውሰድ የወሰነው፡ የጠላትን ኃያልና ደካማ ጎን በትኩረት የገመገመ ረቂቅ የስለላ መረጃዎችን ካጠናና ከመረመረ በኋላ፡ እንዲሁም በደጋማው የጠላት ወረዳ ውስጥ ባካሄደው ተደጋጋሚ የደፈጣ ውጊያ ጠላትን ለማታለልና የጠላትን የትኩረት አቅጣጫ ለማዛባት በመቻሉ ነው።

ከዚህ ትልቅ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ሁለት ወር በፊት፡ የናደው እዝ ኣዛዥ ብሪጋዴር ጀነራል ታሪኩ ያይኔ፡ ለሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት (ሁ.አ.ሰ.) ኣዛዥ ለጀነራል ረጋሳ ጂማ በላከው ደብዳቤ፡ ህዝባዊ ግንባር በናቅፋ ግንባር ላይ ብርቱ የስለላ ጥናት በማካሄድ ላይ መሆኑን ይህም ብርቱ ጥቃት ለመፈጸም እየተዘጋጀ መሆኑን የሚያመላክት እንደሆነና፡ ‘መክት እዝ’ን ለማገዝ ከግንባር ወደ ደጋማው ኤርትራ ውስጣዊ ቀጠናዎች የተሰማሩት ወይም እንዲሄዱ የተደረጉት 15ኛና 22ኛ ክፍለጦሮች ባስቸኳይ እንዲመለሱለት ጥያቄውን አቅርቦ ነበር። ይሁን እንጂ የሁ.አ.ሰ. አዛዥ የሰጠው መልስ፡ “ባለን መረጃና ግምገማ መሰረት፡ በቅርቡ ሻዕብያ ብርቱና ሰፊ ጥቃት ይፈጽማል ብለን አናምንም። ስለሆነም እነዚያ ሁለት ክፍለጦሮች ለግዜው እዚሁ በደጋማው ክፍል ውስጥ ያለንን ስጋት ለማስወገድ እዚሁ በውስጥ ቀጠና እየሰሩ ይቆያሉ። ለማንኛውም ግን ብርቱ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል።” የሚል ነበር።

የሁ.አ.ሰ. አዛዦች “ሻዕብያ በናቅፋ ግንባር የመከላከያ ምሽጉን በማደላደል ላይ እንጂ የማጥቃት እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል አንዳችም ፍንጭ አይታይበትም” የሚል ድምዳሜ ላይ እንዲደርሱ ያደናገራችው፡ አንዴም ህዝባዊ ግንባር ጠላትን ለማደናገርና ለማታለል፡ ከስድስት በላይ ብርጌዶችን በጠላት የውስጥ ቀጠና ማለትም ብደጋው ክፍል አሰማርቶ የደፈጣ ውጊያን በቀጣይ ይፈጽም ስለነበረ አሊያም በታሕሳስ 1987 በናቅፋ ግንባር በተካሄደው መጠኑ አንስተኛ በሆነው ጥቃት የተቆጣጠራችውን አዳዲስ ስፍራዎች፡ ምሽግ በመቆፈር ይዞታውን ማጠናከር ላይ በቀጣይነት ሲንቀሳቀስ ይታይ ስለነበር ነው።

“ደርግን’ በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር ታሪኽ ይቀጥላል!!!

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 23 Mar 2022, 05:15

Meleket wrote:
11 Mar 2019, 04:56
የተአምራዊው ጥቃት አፈጻጸም
1.1 የሁለቱ ተጻራሪ ወገኖች የሰራዊት ዓቅምና የኃይል አሰላለፍ

አስቀድሞ እንደተገለጠው፡ ናደው እዝን መደምሰስ በህዝባዊ ግንባር አመራሮች ዘንድ ለረዢም ግዜ ሲጠናና ዕቅድ ሲነደፍለት የቆየ ጉዳይ ነው። በዚህም መሰረት፡ ይህን ትልቅ የማጥቃት እርምጃ ለመተግበር ረዢም ግዜ የወሰደ ብርቱ የስለላ ጥናት ውጤትን ምርኩዝ ያደረገ ረቂቅ ግምገማ ተካሂዷል። ጠላትን ለማሞኘትና ለማዘናጋትም በደጋማ ክፍል እንዲሁም በግንባሮች ሁሉ ፋታ የማይሰጡ አደናጋሪ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ይደረጉ ነበር።

ይህ የጥቃት ዕቅድ ትግባሬ የዜሮ ሰዓቱ ሲቃረብም፡ ይህን ሰፊ የጥቃት ንድፍ ተግባር ላይ ለማዋል የተመደቡ የህዝባዊ ግንባር ክፍሎች፡ ማለትም ከእግረኛ የ85ኛ፣ 61ኛ፣ 16ኛ፣ 70ኛና 52ኛ ክፍለጦሮች፣ 74ኛ መካናይዝድ ክፍለጦር እንዲሁም የተለያዩ ድጋፍ ሰጪ የስለያ የመሃንዲስ የሎጂስቲክና የህክምና ወዘተ ክፍሎች ወደየተመደበላቸው ተልእኾና ዒላማ አመሩ። በዚህ የጥቃት ውጥን ትግባሬ ላይ የተሳተፉ የህዝባዊ ግንባር የሰራዊት አባሎች በድምር 10,400 እንደነበሩ የዚያን ግዜ ሪፖርቶች ያመለክታሉ።

ለአስር ያህል ዓመታት በተካሄዱት ከባድ ተከታታይ ውጊያዎች ምክንያት ኤርትራ ውስጥ የነበረው ኢትዮጵያ ሰራዊት ቁጥር አሽቆልቁሏል። በዚህም መሰረት የናደው እዝ ከመደምሰሱ ዋዜማ፡ ደርግ ኤርትራ ውስጥ አሰማርቶት የነበረው የሰራዊት ብዛት እስከ 94,000 ይሆን ነበር።

በደጋማ የኤርትራ ክፍሎች የነበረው ‘መክት እዝ’ 30,000፡
በሓልሓል ግንባር መሽጎ የነበረው ‘መንጥር እዝ’ ከ21,000 በላይ
ባርካ የነበረው ‘በርግድ እዝ’ 14,500፣
ድጋፍ ሰጪ የሁ.አ.ሰ. ክፍሎች ከ7,000 በላይ የሰራዊት ቁጥር ነበሯቸው።
ናደው እዝም ከጠቅላላ ዓቅሙ፡ አስቀድሞ በናቅፋ ግንባር በወረደበት ጥቃት ምክንያት ከ4,700 በላይ አባሎቹ በሞት፣ በመቁሰልና በተለያዩ ምክንያቶች ጎድለውበት ስለነበር፡ የሰራዊቱ አባሎች ወደ 16,500 አሽቆልቁሎ ነበር። ውጊያ በተከፈተበት ሰዓት በሂሊኮፕተር አፍዓበት ላይ ተራግፈው የተደረቡትን የ 15ኛ ክፍለጦር ሁለት ሻለቆች በመደመር፡ በጦርነቱ ወቅት የናደው እዝ ሰብኣዊ ኣቕም 18,000 ያህል ነበር። በግንባሩ ተሰልፈው የነበሩት የናደው እዝ ክፍሎች
ከእግረኛው ክፍል 21ኛ፣ 19ኛ፣ እና 14ኛ ክፍለጦሮች፣
29ኛ መካናይዝድ ብርጌድ (ዘርኣይ ደረስ)፣
የ157ኛ መድፈኛ ሻለቃና ሌሎች ድጋፍ ሰጪ ተደራቢ ክፍሎች ናቸው።

ናደው እዝ ታጥቆት የነበረው መሳሪያም፦
54 ታንኮች፣
16 የ130ሚ.ሜ. መድፎች፣
36 የ122 ሚ.ሜ. መድፎች፣
12 የ ቢ.ኤም 21 ተወንጫፊ ሮኬቶች፣
55 ከባድ መሳሪያ የተጠመደባቸው መኪኖች
፣ እንዲሁም በርካታ ሞርታሮች፣ መካከኛ መሳሪያዎችና ከ18,000 በላይ ቀላል መሳሪያዎችን ያጠቃልላል።

(የነጻነት ታጋዮች የማጥቃት ዕቅድ ምን ይመስላል በቀጣይ እንሄድበታለን)
ይህን ሁሉ ኃይል ድባቅ የመቱት የነጻነት ታጋዮች ያልተሸራረፈች ኤርትራን ነጻ ለማውጣት ነበር። ጥቃቱን በፈጸሙበት ቅጽበትም ብርቱ የራስ ሕመም በደደቢት በአዲሳአበባና በክሬምሊን ‘ቤተመንግሥቶች’ ውስጥ ተከስቶ እንደነበረ የጊዜው “የሜትሪዮሎጂ’ መረጃዎች ጠቁመዋል።
:mrgreen:

Fed_Up
Senior Member+
Posts: 22764
Joined: 15 Apr 2009, 10:50

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Fed_Up » 23 Mar 2022, 06:52

ኤርትራዊ መስሎ ለመታየት የሚደረግ አሰልቺው የኣጋሜው Meleket ዝብዘባ:: :oops:

"ለማያቅሽ ሄደሽ ታጠኝ" አሉ ጌቶችህ ሲተርቱ
እኔ በአንት ፈንታ ተሳቅቄ ልሞት ነው::

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 23 Mar 2022, 08:31

ወዳጃችን Fed_Up አንተም ሆንክ እዚህ የሚለቀልቁ ተራ ካድሬዎች ስለ ኤርትራና ኤርትራዊነት ለመናገር ምንም ዓይነት የሞራል ልዕልና የላችሁም፡ ብለናል እኛ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች። እርስዎ ወዳጃችን እንዳይሳቀቁ ብለንም፡ የኤርትራን ህዝብ ኣኩሪ ታሪክ ለዓለም ከማሳወቅ ወደኋላ ኣንልም። አሁን እስቲ የናደው ታሪክ በየዓመቱ ቢዘከር ታሪኩ በአማርኛም በአረብኛም በእንግሊዝኛም አሁንም አሁንም ቢነገር ምንድነው አንተን የሚከነክንህና የሚያብከነክንህ? ለኛ አልገባንም። ቢሆንም ግን ባለህበት ሰላምና ጤና እንመኝልኃለን።
Fed_Up wrote:
23 Mar 2022, 06:52
ኤርትራዊ መስሎ ለመታየት የሚደረግ አሰልቺው የኣጋሜው Meleket ዝብዘባ:: :oops:

"ለማያቅሽ ሄደሽ ታጠኝ" አሉ ጌቶችህ ሲተርቱ
እኔ በአንት ፈንታ ተሳቅቄ ልሞት ነው::

ይህ 34ኛ ኣመት የኣፍዓበት የድል በዓልን ልዩ የሚያደርገው፡ በታሪክ ያልተማረው የራሽያ ትዕቢተኛ ሰራዊት፡ ልዑላዊት ጐረቤት ሃገሩን ሃገረ ዩክሬንን በማንአለብኝነት በመውረር ንጹሓን ዜጎችን በእውርድንብስ በከባድ መሳርያ በመደብደብ ባለበት ወቅት፡ ጀግናው የዩክሬን ህዝብም ዘለንስኪ በተባለ ጀግና በመመራት ለክብሩና ለነጻነቱ ሲል ወራሪውን የራሻ ጦር በመመከት ላይ ባለበት የታሪክ አጋጣሚ ነው። ወራሪ ምን ግዜም ተሽናፊ እንደሆነ ከኛ ከኤርትራዉያን ገድል በላይ ምስክር የለም። አሁን የጦር ጥቅመኞችንም ወዳንጨረጨረው ትረካችን እንቀጥላለን፡ በኤርትራዊ ጭዋነትና ኩራት ጭምር።
:mrgreen:
Meleket wrote:
13 Mar 2019, 03:35

1.2 የጥቃቱ ዕቅድ
ናደው እዝ ይቆጣጠረው የነበረው ቦታ፡ በቅድመ ግንባር እስከ 165 ኪ.ሜ. ርዝማኔ የነበረው ሰንሰለታዊ ምሽግ፡ እንዲሁም ከነዚህ ምሽጎች በስተጀርባም እስከ 70 ኪ.ሜ. ራዲየስ ያካለለ ባጠቃላይ እስከ 12,000 ኪ.ሜ. ስዄር ስፋት የነበረው ቦታ ነው። በዚህ በተጠቀሰው ስፍራ መሽጎ የነበረውን የኢትዮጵያ ማለትም የደርጉን ሰራዊት በሙሉ ፍጹም ከበባ ውስጥ በማስገባት፡ ለመጨፍለቅ የታቀደው ወታደራዊ ንድፍ፡ ስድስት መአዘኖች ወይም የጥቃት አቅጣጫዎች ነበሩት። በዚህ መሰረትም፡ የህዝባዊ ግንባር ሰራዊት በስድስት ምድቦች ተከፍሎ የማጥቃት እርምጃውን ለመጀመር አይምሬ በትሩን አነሳ። አጥቂዎቹ የነጻነት ታጋዮች የተከተሏቸው ስድስት አቅጣጫዎችና ተልእዃቸው የሚከተሉት ነበሩ።

የመጀመሪያው አቅጣጫ
በግራ ክንፍ ማለትም በግንባሩ በስተምስራቅ፡ ‘ቃምጨዋይ’ በተባለው አካባቢ ‘መሸታይ’ ከተባለው ስፍራ በመነሳት ‘ማዕሚደን’ አካልሎ መንጥር ዕዝ እስከ መሸገበት ስፍራ በመዘርጋት የምስራቁን ሜዳማ ክፍሎች ይቆጣጠር የነበረውን የኢትዮጵያን ሰራዊት ማለትም 14ኛ ክፍለጦርንና 29 ሜካናይዝድ ብርጌድን በማጥቃት፡ ‘ማዕሚደን’ በመቆጣጠር በቀጥታ በግራ ክንፍ ወደ አፍዓበት መገስገስ። በዚህ በመጀመሪያው የማጥቃት ኣቅጣጫ የተመደቡት የህዝባዊ ግንባር ሰራዊት አባሎች፡ ከ85ኛው ክፍለጦር ሁለት ብርጌዶች፣ ከ61ኛው ክፍለጦር 87ኛ ብርጌድ ሁለት ሻምበሎች፣ 23ኛው የመካናይዝድ ብርጌድ፣ እንዲሁም አንዳንድ የ63ኛው መካናይዝድ ብርጌድ ክፍሎች ነበሩ።

ሁለተኛው አቅጣጫ
‘ኢትሓልበብ’ና ‘ክርፍ’ በተባሉት ተራሮች መካከል ባለው ሰርጥ ጨለማን ተነን አድርጎ በመነሳት፡ በጠላት ምሽጎች መካከል ሾልኾ በማለፍ፡ ‘ጉድ’ ወደ ተባለው ወንዝ መቀላቀል፡ ከዚያም ወደ ቀኝ በመታጠፍ ‘ሮሬት’ የተባሉትን ተራሮች መውጣት፣ ከዚያም ከፊሉ ሰራዊት ወደ ሰሜን አቅጣጫ በማቅናት በተራራ ቁጥር 1419 እና 1467 ላይ መሽጎ የነበረውን የኢትዮጵይ ሰራዊት በስተጀርባው ማጥቃት፤ የተቀረው ከፊል ሰራዊት ደግሞ አቅጣጫውን በስተደቡብ ‘ሓራስ ሓርማዝ’ ወደ ተባለው ስፍራ በማቅናት ‘ሓርጠጠት’ በተሰኘው ተራራ ላይ መሽጎ የነበረውን የኢትዮጵያ ሰራዊት ማጥቃት፡ በዚህም በ‘ሮሬት’ ተራራዎችና ‘ሕዳይ’ በተባለው ወንዝ አካባቢ መሽጎ የነበረውን 19ኛ ክፍለጦር ከነ ተደራቢ የታንከኛ መድፈኛና ከባድ መሳሪያ እንዲሁም ሞርታረኛ ክፍሎቹ ባጠቃላይ መደምሰስ። በዚህ የጥቃት ዘመቻ የተመደቡት የህዝባዊ ግንባር የነጻነት ታጋይ ሰራዊቶች፡ ከ61ኛው ክፍለጦር 81ኛ ብርጌድ፣ ከ87ኛው ብርጌድ አንድ ሻምበል፣ እንዲሁም አንድ የእግረኛ ከባድ መሳሪያ የመቶ፣ ከ 52ኛው ክፍለጦር ከ24ኛው ብርጌድ አንድ ሻምበል፣ ከ16ኛው ክፍለጦር ከ26ኛው ብርጌድ አንድ ሻምበል ሲመደቡ ከነዚህ በተጨማሪም ‘ሕዳይ’ በተባለው ወንዝ አቅጣጫ እንዲያጠቁ የተመደቡት 34ኛ እና 63ኛ ሜካናይዝድ ብርጌዶች ነበሩ።

ሶስተኛው አቅጣጫ
ከ‘ኣምባ’ እስከ ‘ኣርሃጸት ዓቢ’ የተባሉ ተረተሮች እንዲሁም እስከ ‘ጠልቀሳ’ የተባለው ወንዝ ድረስ ባለው ስትራቴጂያዊ ቦታዎች ላይ መሽጎ የነበረውን የደርጉ 19ኛና 21ኛ ክፍለጦር ክፍሎች ከነተደራቢ ጓዶቻቸው ጋር መደምሰስ። በዚህ ጥቃት ላይ በሞርታርና በመትረየሶች ታግዞ ከፊት ለፊት እንዲያጠቃ ከተመደበው አንስተኛ ኃይል በተጨማሪ፡ ሁሉም በዚህ ምድብ የተደለደሉት ሻምበሎች በጠላት ምሽግ መካከል በከፍተኛ ጥንቃቄ ሾልከው በመግባት፡ ድምጣቸውን አጥፍተው በመጓዝ የኢትዮጵያን ሰራዊት ከበስተጀርባና በጎን በኩል እንዲያጠቁ ተመደቡ። በዚህ የማጥቃት እርምጃ እንዲሳተፉ የተመደቡት የነጻነት ታጋዮች በስተግራ የ70ኛው ክፍለጦር 26ኛው ብርጌድ ኣባላት፡ እንዲሁም በስተቀኝ የ61ኛው ክፍለጦር 11ኛው ብርጌድ አባላት ሲመደቡ፡ በተጨማሪም ‘ፈርኔሎ’ እና “ቀብርጻዕዳ’ በተባሉት ስፍራዎች በኩልም የ34ኛው ሜካናይዝድ ብርጌድ አባላት ተመድበው ነበር።

አራተኛው አቅጣጫ
‘ሸገ’ ከተባለው አካባቢ በመነሳት ‘ኣንደብ’ እና ‘ሓሳይድ’ በተባሉ ስፍራዎች መካከል ሰንጥቆ በማለፍ፤ ‘ሓሳይድ’ን በስተደቡብ አጥቅቶ በመቖጣጠር፣ ከአፍዓበት በስተምዕራብ ወደሚገኙት ስትራቴጂካዊ ቦታዎች መገስገስ፣ ‘ገብገብ’ በተባለው ወንዝና ‘ግሎብ’ እንዲሁም ‘ሽኽናብ’ የተባሉትን ስፍራዎች ከጠላት ይዞታነት ሙልጭ አድርጎ በማጽዳት፣ ‘ሃበሮ’ ከተባለው ስፍራ የሚመጣውን ረዳት የደርግ ሰራዊት መግታት። በዚህ ዕቅድ ትግባሬ ላይ የተሰማሩት የነጻነት ታጋዮች የሰራዊት አባላት የ70ኛዉ ክፍለጦር 10ኛ ብርጌድ ሁሉም አባሎች፣ ከ71ኛው ብርጌድ ደግሞ አንዲት ሻምበል፣ እንዲሁም አንድ እግረኛ የከባድ መሳሪያ ሻምበልና ከ34ኛው መካናይዝድ ብርጌድም አንዳንድ አባላቶች ተመድበዋል።

አምስተኛው አቅጣጫ
የናደው እዝን ለማጥቃት በግንባር በኩል ጥቃቱ በሚሰነዘርበት ሰዓት፡ አፍዓበትንና ከረንን በሚያገኘው መንገድ ሾልኮ በመግባት፡ ከከረን 30 ኪ.ሜ. ርቀት ውስጥ በሚገኙት ስትራቴጂያዊና ለደፈጣም አመቺ የሆኑትን የ’መስሓሊት’ የተራራ ሰንሰለቶችን በመቆጣጠር፡ የናደው እዝ ሊያመልጥበት የሚችልበትን ቀዳዳ ሁሉ በመድፈን ሙሉ በሙሉ ከባባ ውስጥ ማስገባት፡ ከከረንም ረዳት እንዳይደርስለት ማገት፣ ከአፍዓበትም የሚሸሸውን ማንኛውም የኢትዮጵያ (የደርግ) ሰራዊትን ከነ ሙሉ ትጥቁ ሙሉ በሙሉ ቁጥጥር ስር ማዋል። በዚህ የማጥቃት ምድብ ውስጥ የተመደቡት የነጻነት ታጋዮች ክፍሎች፣ 52ኛው ክፍለጦር በሙሉ እንዲሁም አንድ የእግረኛ ከባድ መሳሪያ ሻምበል ነበሩ። ይህ አጥቂ ኃይል፣ ከጠላት ይዞት ውስጥ ማለትም ‘ማይ መደፍ’ ከተባለ አካባቢ በመነሳት ‘ደርሰነይ’ የተባለውን ስፍራ በማለፍ፡ ከከረን አስመራ የተዘረጋውን መንገድ ‘ሽንድዋ’ በተባለው ስፍራ ቆርጦ በማለፍ፡ በ’ምራራ’፣ ‘ዒራዒሮ’ እንዲሁም ‘እምባ’፣ ‘አፍሉቕ’ ኣና ‘እንስ’ የተባሉትን ስፍራዎች በማለፍ፡ ከአፍዓበት ወደ ከረን የሚወስደውን መንገድ እንዲቆጣጠር ነው የተመደበው።

ስድስተኛው አቅጣጫ
ከ‘ሰሜናዊ ባሕሪ’’ ጫካዎች በመነሳት፡ ከአፍዓበት ከተማ በስተምስራቅ ማለትም በ‘ኣዛህራ’ና ‘ጋድም ሓሊብ’ በኩል የነበረን የኢትዮጵያ ሰራዊት ምሽግ በማጥቃት፣ ከግንባሩ በስተቀኝ አቅጣጫ ማለትም ‘ፈልከት’ በተባለው ስፍራ በኩል ከሚመጣው የወገን ሰራዊት ጋር በመተሳሰር አፍዓበት ከተማን መቆጣጠር። ይህ አጥቂ ኃይል ጥቃቱ በተጀመረበት ዕለት፡ በደቡብና ደቡባዊ ምስራቅ የነበረው የደርጉ ሰራዊት እስኪያፈገፍግ ወይም እስኪጠቃ ድረስ ጠብቆ፡ በሁለተኛው ቀን የውጊያ ውሎው ተልእኾውን ለመፈጸም የተመደደ ነው። በዚህ የማጥቃት አቅጣጫ የተሰለፉት የነጻነት ታጋዮች፡ የ85ኛው ክፍለጦር 22ኛው ብርጌድ እንዲሁም 5 እግረኛ የከባድ መሳሪያ የመቶዎች ጋር ነው። ከ61ኛው ክፍለጦርም የ13ኛው ብርጌድ 2 ሻምበሎችና አንድ የከባድ መሳርያ ሻምበልም ይህን ተልዕኾ ለማሳካት ተመድቧል።

የማጥቃት ዕቅዱ ይህን ሲመስል፡ በሚቀጥለው ክፍል ከመጋቢት 17-19 የተካሄደው ውጊያ ምን ይመስላል የሚለውን እናብላላለን እናብራራለንም!

ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ፡ ዲጅታሎቹን ያስመረረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ ይቀጥላል
:mrgreen:

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 23 Mar 2022, 11:14

ምስሉ ላይ የሚታዩት በኤርትራዉያን ታጋዮች የተማረኩ የልዕለኃያል ሃገር ነኝ የምትለው የሶቭየት ህብረት የጦር ኣማካሪ መኮንኖች ናቸው። ድንቄም ኣማካሪ! :mrgreen:

ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ፡ ዲጅታሎቹን ያስመረረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው ኤርትራዊ በትር - ታሪክ ይቀጥላል :mrgreen:
Meleket wrote:
15 Mar 2019, 03:25
1.3 የውጊያው አፈጻጸም ሂደት (17-19 መጋቢት)

የህዝባዊ ግንባር ሰራዊት አስቀድሞ በተጠቀሰው አሰላለፍ፡ መጋቢት 17 1988 ማለዳ በአምስቱ ማእዘኖች የማጥቃት እርምጃውን ጀመረ። ምንም እንኳን የኢትዮጵያ (የደርጉ) ሰራዊት በርትቶና ወጥሮ ለመዋጋት ቢሞክርም፡ ቀኑን ሙሉ በቀጠለው ውጊያ፡ የመጀመሪያና ሁለተኛ የመከላከያ ወረዳውን ለቆ ሲያፈገፍግ፡ ከግንባሩ ውጪ ማለትም በተለያዩ ማእዘኖች እንዲያጠቁ ተመድበው የነበሩት የነጻነት ታጋዮች፡ በጠላት ወረዳ ውስጥ ከከረን አፍዓበት የሚወስደውን መንገድ እንዲያጠቁ የተመደቡትም ጭምር ዓላማቸውን በእቅዱ መሰረት አሳኩ። በኢትዮጵያ ሰራዊት ወረዳ ውስጥ እንዲያጠቃ የተመደበው የነጻነት ታጋዮች 52ኛ ክፍለጦር፣ በዚሁ ዕለት ‘መስሓሊት’ በተባለ ስፍራ በመመሸግ፡ ከከረን ወደ ኣፍዓበት ለረዳትነት የተንቀሳቀሰውን የኢትዮጵያ ሰራዊት ሲከላከል ዋለ።

ውጊያው በሚካሄድበት በሁለተኛው ቀን ማለትም መጋቢት 18፡ በአምስቱ ማእዘኖች የጥቃት እርምጃውን ያካሄደው የነጻነት ታጋዮች ኃይል፡ ብርቱ ረሃብ፣ ጥምንና ድካምን ተቆቁሞ፡ የጎደለውን መሳርያና ጥይት ከኢትዮጵያ ሰራዊት እየማረከና እየተጠቀመ፡ በቅጽበት በመገስገስ፡ ሰፊ ቦታዎችን ተቆጣጠረ። የደርጉ ማለትም የኢትዮጵያ ሰራዊትም በዚህ ሃያልና ፋታ የማይሰጥ የማጥቃት እርምጃ አደረጃጀቱ ተዛብቶ፡ አዛዥና ታዛዥ ተደበላልቆ፡ የእዝ ሰንሰለት ተጥሶ፡ አብዛኛው ክፍሉ ቅጥ ባጣ መልኩ ወደኋላ ለመሸሸት ተገደደ።

ናደው እዝ ሲደመሰስ እጅግ ብርቱ ውጊያ የተካሄደት ስፍራ ‘ሞጋዕ ቀጣሪት”ና ‘ቃምጨዋ’ ይባላሉ። የኢትዮጵያ ሰራዊት አዛዦች፡ ከተራራማ ገዢና ስትራቴጂያዊ ስፍራዎች ተገፍቶ ብትንትኑ ወጥቶ ወደ ተጠቀሱት ሰርጦችና ጅረቶች የወረደውን እግረኛ ሰራዊት፡ ዳግም ተደራጅቶ የከባድ መሳርያ መሽጎበት የነበረውን የደጀን ቦታቸውን ሊከላከልላቸው እንደማይችል በመገምገም፡ እዚያ አካባቢ የነበረውን ማንኛውም መሳርያቸው እንዳይማረክባቸው በአፋጣኝ እንዲያፈገፍጉ ወሰኑ። በዚህም መሰረት ከ 70 እስከ 80 የሚሆኑ ታንኮችና ተሽከርካሪዎች፡ በቀትር ወደ አፍዓበት ጉዟቸውን ተያያዙት። ነገር ግን በ15፡30 አካባቢ እነዚህ በርካታ ታንኮችና ተሽከርካሪዎች፡ ‘ዓሽሩም’ የተባለውን ዳገት ተሰልፈው ይወጡ በነበሩበት ወቅት፡ በ‘ሕዳይ’ ወንዝ በኩል አልፈው ሁነኛ ቦታ ላይ ተዘጋጅተው ይጠብቁ በነበሩ የነጻነት ታጋይ ታንከኞች ዒላማ ውስጥ ገቡ። ከነጻነት ታጋዮች 34ኛ ታንከኛ ብርጌድ ታንኮች አንዷም፡ በርቀት በተኮሰችው ጥይቷ፡ ዓሽሩም ጫፍ ላይ ደርሳ የነበረችን አንዲት ቢ.ኤም. 21 ተወንጫፊ ሮኬት የጫነች መኪናን አቃጠለች። ሁለተኛዋ ከታንኳ የተተኮሰው ጥይትም፡ አቀበቱ መሃል የነበረችን አንዲት ታንክ አቃጠለች። በዚህም ምክንያት “ዘርአይ ደረስ” ተብሎ የሚጠራው የኢትዮጵያ ሰራዊት እጅግ የሚመካበት 29ኛው መካናይዝድ ብርጌድ ተሽከርካሪዎችና ታንኮች መፈናፈኛ መንገድ አጥተው ለብርቱ አደጋ ተጋለጡ።

ይህን ያህል ከባድ መሳርያ የጫኑ መኪናዎችና ታንኮች ማፈግፈጊይና መውጫ ቀዳዳው ሲጠፋቸው፣ ውጊያውን ይመራ የነበረው የኢትዮጵያ (ሁ.አ.ሰ.) አዛዥ ሜጀር ጀነራል ውበቱ ጸጋየ፣ ያ ሁሉ የታገተውና ወጥመድ ውስጥ የገባው ከባድ መሳርያና ታንክ በነጻነት ታጋዮች ቁጥጥር ስር እንዳይገባ፡ የውጊያ አውሮፕላኖች እንዲያጋዩት መመሪያ ሰጠ። በዚያን ቀውጢ ሰዓትም፡ የወገኑን ከባድ መሳርያዎችና ታንኮች እንዲያጋይ ትእዛዝ የተሰጠው የውጊያ ጄት አብራሪም፡ “አዬ መንግስት ሲወድቅ” ብሎ ሲናገር በሬዲዮ ሞገድ ተጠለፈ። በርግጥ ያ እጅግ ሰፊ የሆነው ደምሳሽ የማጥቃት እርምጃ የኢትዮጵያ ሰራዊት ላይ ያሳረፈው ግዙፍ ጠባሳ እጅጉኑ ጎልቶ የታየው ‘ዓሽሩም’ በተባለው ዳገት ላይ ነው።

በመጋቢት 18 የውጊያ ውሎም፡ ሲሶው የኢትዮጵያ ሰራዊት ዓቅም ተወቅጦ፡ በግምባር በኩልም ያጠቃ የነበረው የነጻነት ታጋዮች ክፍልም 40 ኪ.ሜ. ወደፊት ገፍቶ፡ የደርጉን ሰራዊት አሉ ከሚባሉት ስትራቴጂያዊ ተረተሮች ጠራርጎ ሲያወርደው፡ በግራና ቀኝ ክንፎች ያጠቁ የነበሩት የነጻነት ታጋዮች ክፍሎች ደግሞ፡ አፍዓበት ከተማ መዳረሻ አካባቢን ተቆጣጥሮ አደረ። ከበስተኋላ ከከረን ወደ አፍዓበት የሚወስደውን መንገድ ግጥም አርጎ ዘግቶት የዋለው የነጻነት ታጋዮች 52ኛ ክፍለጦርም፡ ከከረን ለረዳትነት ይመጣ የነበረን ግዙፍ የደርግ ሰራዊት በብርቱ መስዋእትነት መክቶት ዋለ። ስለሆነም የናደው እዝ በሁሉም አቅጣጫዎች እየተነዳ አፍዓበት አካባቢ እጅግ ጠባብ ቀለበት ውስጥ ለመከበብ ተገደደ።

በሶስተኛው ቀን ማለትም መጋቢት 19 1988 ማለዳ 5፡30 ላይ አፍዓበትን ከቦ ያደረው የነጻነት ኃይሎች ታጋይ ሰራዊት የመጨረሻ የጥቃት እርምጃዎቹን ሰነዘረ። በሁለቱ የማጥቃት ቀናት ከባድ ኪሳራ አጋጥሞት እጅግ የተዳከመው የኢትዮጵያ (ደርጉ) ሰራዊት፣ ለአጭር ጊዜ ተቃውሞ በማድረግ ለመከላከል ቢሞክርም፡ የነጻነት ታጋይ ሃይሎች የጥቃት እርምጃ እጅግ ከባድ ስለነበረ፡ የደርጉ ሰራዊት ንብረቱን እያቃጠለ መሸሸት ጀመረ። በከተማዋ ምስራቅና ደቡባዊ ምስራቅ አቅጣጫ ተጠግቶ ያደረው የነጻነት ሃይሎች ተዋጊ ሰራዊትም ማለዳ 9:00 (3፡00) አፍዓበት ከተማ ገስግሶ ገባ። በሰሜንና በሰሜናዊ ምዕራብ ሲገሰግስ ያደረው የነጻነት ታጋዮች ተዋጊ ኃይልም፡ ከረፋዱ 10፡00 (4፡00) ተልእኾውን ፈጽሞ አፍዓበት ከተማ በድል ገባ።

አፍዓበትን ለመቆጣጠር ማለዳ ‘ሻባይ መንደር’ በተባለው ስፍራ በተካሄደው አጭርና ብርቱ ውጊያም፡ የ61ኛው ክፍለጦር 87ኛ ብርጌድ 3ኛ ሻምበል፡ 3 የሶብየት ሕብረት ከፍተኛ የጦር አማካሪዎችንና ሌሎች ኢትዮጵያዉያን መኮንኖችንን ማረከች።

ከዚህ በኋላም በአፍዓበትና በአካባቢዋ በተደረገ ውጊያ ከሞትና ከመማረክ አምልጦ፡ ጥቂት ታንኮቹንና ተሽከርካሪዎችን ይዞ ወደ ከረን ለማምረጥ የሞከረ የኢትዮጵያ ሰራዊት፡ የነጻነት ታጋዮች 52ኛው ክፍለጦር አዘጋጅቶት በቆየ ወጥመድ ውስጥ ስለገባ፡ ንብረቱን ጥሎ እግሬ አውጪኝ ብሎ በ ‘ግዝግዛ’ ‘ቀልሃመትና’ ‘ሂካኖ’ በተባሉት ስፍራዎች ብትንትኑ ወጣ።

የናደውን እዝ የመደምሰስ ብርቱ ውጊያም፡ መጋቢት 19 1988 ከቀትር በኋላ ‘ግዝግዛ’ በተባለው ስፍራ በተካሄደ የመጨረሻ ውጊያም ተደመደመ። ከውጊያው በፊት ከነጻነት ታጋይ የሰራዊት አዛዦች አንዱ እንደተነበየውም፡ ደርጉ እጅግ ይመካበት የነበረው ብርቱ የሰራዊቱ ክፍል የሆነው “ናድው እዝ” የቀብር ስነስርዓቱ በኤርትራዉያን ታጋዮች ድል ተፈጸመ

የኤርትራ የነጻነት ታጋዮች፡ አስር ዓመታት ያህል ያለመታከት በናቅፋ ግንባር ያደርጉትን የመመከት ተልዕኾ አገባደው፡ ‘መስሓሊት’ በተባለው ስፍራ አካባቢ “ የከረን ግንባር” የሚባል አዲስ ግንባር በመክፈት፡ ወደ አዲስ የማጥቃት ስትራቴጂካዊ መድረክ የሚያሸጋግር የበላይነቱን ጨበጡ።

በቀጣይ ናድው እዝን የመደምሰሱ ተልእኾ በኢትዮጵያ ሰራዊት ላይ ያሳደረው ተጽእኖና የዚህን ጦርነት ልዩ ገጽታ እናያለን።

ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ፡ ዲጅታሎቹን ያስመረረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው ኤርትራዊ በትር - ታሪክ ይቀጥላል :mrgreen:

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 24 Mar 2022, 08:49

Meleket wrote:
18 Mar 2019, 09:49
የናደው እዝን የደመሰሰው የማጥቃ እርምጃ አስተዋጽኦና ብርቅነቱ

የናደው እዝን ለመደምሰስ የተካሄደው የማጥቃት እርምጃ፣ በኤርትራ ህዝብ የነጻነት ትግል ታሪክ ውስጥ በዓይነቱም ሆኑ በውጤቱ እጅግ ልዩ ደማቅና አንጸባራቂ ወታደራዊ የድል ታሪክ ነው። ይህን ድል ልዩና ብርቅ የሚያደርጉ ምክንያቶችም፡ አንድ እጅግ ግዙፍ የሆነን ጨቋኝ ሰራዊትን ሙሉ በሙሉ ከበባ ውስጥ በማስገባት ለወሬ ነጋሪ እንኳን ሳታስቀር ሙሉ በሙሉ የመደምሰስ ሂደት በመከናወኑ ነው። ከዚህ የማጥቃት እርምጃ በፊት የነበረው መድረክ፡ የነጻነት ታጋዮች በኢትዮጵያ ሰራዊት ላይ ብዙ ግዙፍና ጥቃቅን ጥቃቶችን ያካሂድ የነበረ ቢሆንም እንኳን፡ ሁሉም እነዚህ የማጥቃት እርምጃዎች፡ ጠላትን በመገፍተርና በመግፋት ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ለመቆጣጠር ያተኮሩ ነበሩ እንጂ እንደዚህኛው የጥቃት እርምጃ ጠላትን ቀለበት ውስጥ በመክበብ ሙሉ በሙሉ ለመደምሰስ ያለሙ አልነበሩም።

የነጻነት ታጋዮች ሃይል ከ1978 አጋማሽ ጀምሮ ለአስር አመታት የተካሄደን ረዢም የህልውና ውጊያ፡ ከጠላት በርካታ መሳሪያዎችና ታንኮችን በመማረክ የተኩስ ብቃቱን ለማጎልበት በቅቷል። ናደው እዝን በመደምሰሱም፡ የተኩስ አቅሙን ይበልጥ የሚያጎለብቱ፡ ከዚያ በፊት ማርኮ የማያቃቸውን የ130 ሚ.ሜ. መድፍና ቢ.ኤም 21 ተወንጫፊ ሮኬት ሚካይሎችን ሲማርክ፡ ከ50 በላይ ታንኮች የሚገኙባቸው በርካታ መሳሪያዎችንና ጥይቶችን ለመማረክ ችሏል። ከዚህም በተጨማሪ፡ የናድወ እዝን በመደምሰስ ሂደት፡ የነጻነት ታጋዮች ለመጀመሪያ ግዜ ሶስት የሶቭየት ህብረት ዜጋ የሆኑ የጦርነት አማካሪዎችን ለመማረክ ችለዋል።

ይህ ግዙፍና ቅጽበታዊ የማጥቃት እርምጃ በደርጉ ስርዓት ውስጥ ከፍተኛ ነውጥንና ሽብርን ፈጥሯል። በመሆኑም ከጥቃቱ ማግስት ማለትም መጋቢት 31 1988 በተካሄደ አስቸኳይ የኢ.ሰ.ፓ ማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ወቅት፡ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅና የክተት አዋጅ ለማውጣት ተገዷል። መንግስቱ ኃይለማርያም በስብሰባው ባሰማው ንግግርም፡ የኢትዮጵያ ህልውና ስጋት ውስጥ መውደቁን በመግለጽ፡ “ጥያቄው ወንበዴዎች ይጥፉ ወይስ እኛ እንጥፋ ነው?” በማለት ደንፍቷል። በዚያ ወቅት በወጣው የክተት አዋጅም፡ በተለያየ ምክንያት ከሰራዊት ተሰናብተው የነበሩ የሰራዊቱ መደበኛ አባላት እንዲሁም የብሄራዊ ውትድርና አገልግሎት አባላት፡ ወደ ሰራዊቱ እንዲመለሱ ሲደረግ፡ ስልጠና ላይ የነበሩት 5ኛ ዙር የብሄራዊ አገልግሎት ወታደሮች በአጭር ግዜ ስልጠናቸውን አገባደው ቅድመ ግንባር ውስጥ እንዲገቡ ተደርጓል።

የደርጉ መሪ መንግስቱ ኃይለማርያምም በዚያን ሰሞን ከሶማሊያው መሪ ከሲያድ ባረ ጋር በጥድፊያ የሰላም ስምምነት እንዲፈርም ያስገደደውም ይህ የናደው እዝ በመደምሰሱ የተገኘ ፍሬ ነው። ያኔዉኑም በምስራቅ ከነበረው ሰራዊቱ ግዙፍ ክፍሉን ወደ ኤርትራ አጓጉዟል። በትግራይና በምእራብ ኢትዮጵያ የነበሩትን የ3ኛ 9ኛና 10ኛ ክፍለጦሮችንም ወደ ኤርትራ በጥድፊያ አጓጉዟል። ደርጉ ትግራይ ውስጥ ለጥበቃነት ያቆየው የሰራዊት ዓቅሙ በጥቂት ከተሞች ብቻ በመወሰኑ፡ ብዙው የትግራይ ክፍል በቀላሉ ከደርጉ ቁጥጥር ውጭ ሆነ። (ትግራይ ነጻ የምትወጣው ኤርትራ ውስጥ በተካሄደ ውጊያ ወላፈን አማካኝነት ነው ማለት ነው።) በቅጽበት ደርግ ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ወደ ኤርትራ ያጋዘው የሰራዊት ብዛት ከ90,000 በላይ ሆኖ ነበር።

ከዚህ በተጨማሪም ደርጉ፡ በምዕራብ ኤርትራ ከከረን እስከ ተሰነይ አሰልፎት የነበረው “በርግድ እዝ’ የተባለው ሰራዊቱ በቅጽበት እንዲያፈገፍግ ተገዷል። በምስራቅም የነጻነት ታጋዮች ሳህልን ከሰሜናዊ ባሕሪና የሰምሃር ሜዳዎች ጋር የሚያገናኘውን ሰፊ ቦታ ለመቆጣጠር ችለዋል። እነዚህን ቦታዎች መቆጣጠራቸውም በቀጣይነት “ፈንቅል” የተባለውን ልዩ ጥቃትና ብርቅ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ያስገኘን ጥቃት ለመሰንዘር በር ከፍቷል።

ናደው እዝን ከደመሰሰ በኋላ የነጻነት ታጋዮች ኃይል የጨበጠውን ድል ለማስጠበቅና ይበልጥም ለማስፋት ይችል ዘንድ፡ በሓልሓል ግንባር ላይ መሽጎ በነበረው “መንጥር እዝ’ ላይ ከፍተኛ አይምሬ ጥቃትን በመሰንዘር ከባድ ኪሳራ በደርጉ ላይ አድርሶ ሰፊ ቦታዎችን ሲቆጣጠር፣ በከረን አካባቢም ተደጋጋሚ የማጥቃት እርምጃዎች በመሰንዘር፡ አዲሱን የመከላከያ ወረዳውን ለማደላደል ችሏል። የደርጉም የነጻነት ታጋዮች የተጎናጸፉትን ድል ለመቀልበስ ከየቦታው አሰባስቦ ባመጣውን ግዙፍ ሰራዊት አድርጎ በአዲሱ የከረን ግንባር በኩል ሰፊ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ ወሰደ። በሮራ መንሳዕና እንሲ፡ በግልንዲ፣ ግዝግዛ፣ ዓጋመትና እንዲሁም በዓንሰባ ወንዝና ሓልሓል በኩልም ለወራት የዘለቀ ብርቱ ውጊያ ተካሄደ። ደርጉ በግንባር በኩል ያካሂደው ከነበረው ውጊያ በተጨማሪ የ102ኛ አየር ወለድ ሰራዊቱን በስውር አንቀሳቅሶ፡ በምስራቃዊው ሜዳማ ቦታዎች በኩል ተዟዙሮ ወደ አፍዓበት የመግባት ያለመ የከሸፈ ጥቃትን ሰንዝሮ ነበር። በዚህ ያልተጠናና የጥድፊያ የጥቃት እርምጃ፣ ክፍለጦሩ በሙሉ ገና ጥቃት እንኳን ሳይሰነዝር፡ በውሃ ጥምና በረዢም ጉዞ ተሸንፎ፡ ምንም ፍሬ ሳያፈራ ለሞትና ለምርኾኛነት ተዳርጓል።

በወታደራዊ ስትራቴጂ አኳያ ናደው እዝን የመደምሰሱ ሂደትና ተጽዕኖው ሊገለጽ የሚችለው፡ ቀጥሎ ከተካሂዱት የማጥቃት እርምጃዎችና የመልሶ ማጥቃት ውጊያዎች ጋር በሰፊ ዓውድ ነው። በዚህ ለወራት በቆየ የደርጉ የማጥቃትና የመልሶ ማጥቃት ውጊያ ወቅት፡ ደርጉ የከሰረው የሰው ኃይልና ዓቅም፡ ናደው እዝን በመደምሰስ ሂደት ከከሰረው ቢበዛ እንጂ አያንስም። በነዚህ ውጊያዎች የነጻነት ታጋዮች ናደው እዝን በመደምሰስ ሂደት የተቆጣጠሯቸውን ሰፊ ቦታዎች ለማቀብ መቻላቸው፡ ደርጉም ብዙ የማጥቃት እርምጃዎችን ቢሰነዝርም ፋይዳቢስ ሆኖ በመቅረቱ፡ ወታደራዊው ሚዛን ሙሉ በሙሉ ወደ ኤርትራዉያን ታጋዮች ማጋደሉን አጉልቶ የሚያሳይ ነው። ናደው እዝን ለመደምሰስ የተሰነዘረው ብርቱ በትር መላዋን ኢትዮጵያን የናጠ፡ (ወያኖችንም በፍራት አንቀጥቅጠው እንደነበሩ ተራኪው አልገለጸውም፡ እኛም ይሁና ብለን ታዝበነዋል) ተጽዕኖው እስከ ሞቃዲሾና የሶቭየት ህብረት ቤተመንግስት ክሬምሊን ድረስ የደረሰ ነበር። ይህም ሲባል ከናደው እዝ መደምሰስ በኋላ ሶስት ከፍተኛ መኮንኖቿ በውጊያው የተማረኩባት ሶቭየት ህብረትም ብትሆን፡ ደርጉ እንደማያሸነፍ ገምግማለች። ልክ በዚያ የታሪክ መድረክም በሶቭየት ህብረት ውስጥ የመጣው የፖሊሲ ለውጥ ወይም ተሃድሶው ተጨምሮበት የክሬምሊን ሰዎች ከደርጉ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት አቀዝቅዘውት ነበር።

ናደው እዝን የመደምሰስ ውጊያ፡ ደርጉ የኤርትራዉያን ታጋዮችን እንቅስቃሴ ለመግታት የነበረውን ህልም ሙሉ በሙሉ ያበነነ፡ የኤርትራ ነጻነት በፍጹም አይቀሬ መሆኑን ለዓለም ግልጽ ያደረገ ድል ነው። ስለሆነም ከናደው እዝ መደምሰስ በኋላ የኤርትራ ጉዳይ በዓለም የዜና መድረክ ውስጥ ትልቅ ትኩረት አግኝቶ ነበር። ታዋቂው የታሪክ ተመራማሪና ጸሓፊው እንግሊዛዊው በዚል ደቪድሰን የጦርነቱን ውጤት በዓይኑ ከታዘበ በኋላ “ከድየን ብየን ፉ በኋላ፡ በአንድ የነጻነት እንቅስቃሴ የተከናወነ ግዙፍ ወታደራዊ ኦፕሬሽን” በማለት የኤርትራዉያን ታጋዮችን ድል ገልጾታል። የድየን ብየን ፉና ናደው እዝን የመደምሰስ ውጊያዎች በተጽዕኗቸው ማለትም የገዢዎችን ዕድሜ በማሳጠር ረገድ ተመሳሳይ ቢሆኑም እንኳን፡ እንደ ወታደራዊ ክንውን ግን ናደው እዝን የመደምሰስ ሂደት ከድየን ብየን ፉ’ዉ እጅግ የላቀና የገዘፈ ነው። ከዚህ የኤርትራዉያን ድል በኋላ በርካታ ሃገሮች የኤርትራ ጉዳይ ሰላማዊ መፍትሄ እንዲያገኝ ጥሪ አድርገዋል። ደርጉም አስቀድሞ አሻፈረኝ ሲል እንዳልነበረ የሰላም ውይይትን ለማድረግ ተገዷል።

ምንም እንኳን የታሪኩ ጸሃፊ ( ታጋይ ሰለሙን በርሀ) ከዚህ ብርቅ የኤርትራዉያን ታጋዮች ድል አንጻር የሕወሃትን መደናበር በቅጡ ባያቀርበውም ላደረገው ታሪክን በበኩሉ የመመዝገብ እርምጃ ምስጋናችንን እናቀርብለታለን።

ይህን በመሰለ የበርካታ ዓመታት ውጊያ ነጻ የወጣችን ልዑላዊት ሃገር በመደመር ይሁን በማባዛት ስሌት ‘አፈፍ’ ለማድረግ የምትቋምጡ ጅሎች ካላችሁ ደግሞ ህልም ወይም የቀን ቕዥት መሆኑን ለመግለጽም እንወዳለን። ህወሃቶችም የኤርትራን ህዝብ የተባበረ ጡንቻና የኤርትራ ህዝብን ትዕግስት በደንብ አድርጋችሁ ታውቁታላችሁ አግአዚ ይሁን ትግራይ ትግርኝ ይሁን ሌላ ፍልስፍና ኤርትራዉያንን አያወናብድም፡ ይልቅ ካርታችሁን አሻሽላችሁ መሬታችሁ ያልሆነን መሬት ለባለቤቱ ለኤርትራ ህዝብ በሰላም አስረክባችሁ በንስሃና በፍቅር ኑሩ ለማለት ነው። በሚገባችሁ ቋንቋ ግልጽ ለማድረግ “ናይና አይንህብይ ላይ እንዳማትና'ለ ኣይንደልይ!!!”


ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ፡ ዲጅታሎቹን ያስመረረ- ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ ዘላለም ይኖራል እየተነገረ!!!
ከዚህ ታሪክ ምን እንማራለን ከተባለ፡ አንድ ነጻነቴን ያለ ህዝብ የተለያዩ ኃይሎች ተቀናጅተው ሊደመስሱት ቢሞክሩም እንኳ፡ በጽናት ከታገለ ማንኛውንም ኃይል ማሸነፍ እንደሚችል ነው። ኤርትራውያን በሶቭየት ህብረት አጋርነትና አማካሪነት እስከ አፍንጫው የታጠቀውን የደርግ ሰራዊት በቅጽበት በመደምሰስ፡ የሶቭየት ኅብረት የጦር አማካሪዎችን ሳይቀር ለመማረክ የበቃነው፡ የነጻነት ትግላችን ፍትሓዊና ቅኑ ስለነበረ እኛም ቁርጠኝነት ስላሳየን ብቻ ነው። አሁንም ልዑላዊት የሆነችውን ሃገረ ዩክሬን በመውረር፡ "ታላቂቱን ሩሲያ ዳግም የመመስረት የቀን ቅዥት" ወፈፌውን ፕረዚደንት ፑቲን ስለተጠናወተው፡ በከባድ መሳርያ እውርድንብሱን በመደብደብ "ታላቂቱ ሩሲያ" የምትመሰረት ቢመስለውም እንኳ፡ ፍትሓዊው የዩክሬን ህዝብ ትግል ፍሬ አፍርቶ፡ እንደ ኤርትራ ህዝብ ሶቭየቶችን አሳፍሮ በሰላም የሚኖርበት ግዜ ሩቅ እንዳልሆነ ነው።

"የታላቂቱ ትግራይ ህልም" = "የታላቂቱ ኢትዮጵያ ህልም" = "የታላቂቱ ሩስያ ህልም" ሁሉም ተመሳሳይ የመስፋፋትና ግዛትን የማስፋፋት ህልሞች፡ በህዝቦች ይሁኝታ ካላገኙ፡ የቀን ቅዠት እንደሆኑ፡ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች በኤርትራዊ ጭዋነትና ኩራት ለጠላትም ለወዳጅም ግልጽ ማድረግ ታሪካዊ ኃላፊነታችንን መወጣት ማለት ነው። :lol:

የከርሞ ሰው ይብለንና፡ ራሻ ልኳን አውቃ፡ የዩክሬን ህዝብም በገዛ ሃገሩ ያሻውን የሚያደርግበት ዘመን እንደሚመጣ በልበ ሙሉነት በመግለጥ፡ የጦር ጥቅመኞችንና የወራሪ ደጋፊዎችን በመጠየፍ ጽሑፋችንን ደመደምን፡ እኛ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች።
:mrgreen:

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 25 Mar 2022, 10:48

የሶብየት ኅብረት መኮንኖች የተማረኩበትን ኤርትራዊውን የአፍዓበት ድል ስናከብር፡ 'ምናባዊውን' የዘለንስኪንና የወፈፌው ፑቲንን ንግግርም እናስታውሳለን

ወፈፌው ፑቲንም ኣለ፦ “ዩክሬኖች በገዛ ሃገራችሁ ለእኔ ስገዱ፡ ሰጥ ለጥ ብላችሁ ተገዙ”

ዘለንስኪም መለሰ፦ “ሂድ ራቅ፡ እኛ ለፈጣሪ እንጂ ለማንም ወራሪ ወፈፌ የምንሰግድ ህዝብ ኣይደለንም!”

"የታላቂቱ ትግራይ ህልም" = "የታላቂቱ ኢትዮጵያ ህልም" = "የታላቂቱ ሩስያ ህልም"

ድል ለሰፊው የዩክሬን ህዝብ!:mrgreen:

Misraq
Senior Member
Posts: 15015
Joined: 27 Sep 2009, 19:43
Location: Zemunda

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Misraq » 25 Mar 2022, 13:53

Agamew Meleket,

you are a very foolish agame :lol: :lol: Not only we see your exposed arrsse, we can see through your aarrsseehole together with the bacterias and all worms in your rectum :lol:

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 26 Mar 2022, 03:38

ኣዬ Misraq ኣንቺ ደግሞ ማን የሚሉሽ “ጥቅመኛ ተንጨርጫሪ” ነሽ ባክሽ?

ታላቂቱ ትግራይ ህልም ነች! = ታላቂቱ ኢትዮጵያም ህልም ነች! = ታላቂቱ ሩሲያም ህልም ነች! :mrgreen:

ማለታችን ቅር ኣሰኘሽ እንዴ። ለወፈፌ ጥብቅና የሚቆም ወፈፌ ብቻ እንደሆነ መቼም ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲሁም ሰፊው የኤርትራ ህዝብ እንደማይስተው፡ እኛ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች እናረጋግጥልሻለን። ኢ ና መ ሰ ግ ኒ ሻ ሎ ን! :lol:

ድል ለሰፊው የዩክሬን ህዝብ!
:mrgreen:

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 28 Mar 2022, 08:25

የዩክሬኑ "ዓሽሩም" ታሪክ እንደወረደ ከ https://www.theguardian.com/world/2022/ ... g-for-kyiv ታሪክ እየተደገመ ነው ያልነው ያለነገር ኣይደለም።
www.theguardian.com wrote:The drone operators who halted Russian convoy headed for Kyiv
Special IT force of 30 soldiers on quad bikes is vital part of Ukraine’s defence, but forced to crowdfund for supplies
Special IT force of 30 soldiers on quad bikes is vital part of Ukraine’s defence, but forced to crowdfund for supplies

Ukrainian drone brigade claims to have stopped 40-mile column of Russian tanks

Julian Borger
Mon 28 Mar 2022 05.00 BSTLast modified on Mon 28 Mar 2022 12.10 BST
One week into its invasion of Ukraine, Russia massed a 40-mile mechanised column in order to mount an overwhelming attack on Kyiv from the north.
But the convoy of armoured vehicles and supply trucks ground to a halt within days, and the offensive failed, in significant part because of a series of night ambushes carried out by a team of 30 Ukrainian special forces and drone operators on quad bikes, according to a Ukrainian commander.

The drone operators were drawn from an air reconnaissance unit, Aerorozvidka, which began eight years ago as a group of volunteer IT specialists and hobbyists designing their own machines and has evolved into an essential element in Ukraine’s successful David-and-Goliath resistance.

However, while Ukraine’s western backers have supplied thousands of anti-tank and anti-aircraft missiles and other military equipment, Aerorozvidka has been forced to resort to crowdfunding and a network of personal contacts in order to keep going, by getting hold of components such as advanced modems and thermal imaging cameras, in the face of export controls that prohibit them being sent to Ukraine.

The unit’s commander, Lt Col Yaroslav Honchar, gave an account of the ambush near the town of Ivankiv that helped stop the vast, lumbering Russian offensive in its tracks. He said the Ukrainian fighters on quad bikes were able to approach the advancing Russian column at night by riding through the forest on either side of the road leading south towards Kyiv from the direction of Chernobyl.

The Ukrainian soldiers were equipped with night vision goggles, sniper rifles, remotely detonated mines, drones equipped with thermal imaging cameras and others capable of dropping small 1.5kg bombs.

“This one little unit in the night destroyed two or three vehicles at the head of this convoy, and after that it was stuck. They stayed there two more nights, and [destroyed] many vehicles,” Honchar said.

A drone is assembled by the Aerorozvidka unit. Photograph: Aerorozvidka
The Russians broke the column into smaller units to try to make headway towards the Ukrainian capital, but the same assault team was able to mount an attack on its supply depot, he claimed, crippling the Russians’ capacity to advance.
“The first echelon of the Russian force was stuck without heat, without oil, without bombs and without gas. And it all happened because of the work of 30 people,” Honchar said.

The Aerorozvidka unit also claims to have helped defeat a Russian airborne attack on Hostomel airport, just north-west of Kyiv, in the first day of the war, using drones to locate, target and shell about 200 Russian paratroopers concealed at one end of the airfield.
“That contributed largely to the fact that they could not use this airfield for further development of their attack,” Lt Taras, one of Honchar’s aides, said.

Not all the details of these claims could be independently verified, but US defence officials have said that Ukrainian attacks contributed to the halting of the armoured column around Ivankiv. The huge amount of aerial combat footage published by the Ukrainians underlines the importance of drones to their resistance.

The unit was started by young university-educated Ukrainians who had been part of the 2014 Maidan uprising and volunteered to use their technical skills in the resistance against the first Russian invasion in Crimea and the Donbas region. Its founder, Volodymyr Kochetkov-Sukach, was an investment banker who was killed in action in 2015 in Donbas – a reminder of the high risks involved. The Russians can latch on to the drone’s electronic signature and quickly strike with mortars, so the Aerorozvidka teams have to launch and run.

Honchar is an ex-soldier turned IT marketing consultant, who returned to the army after the first Russian invasion. Taras was a management consultant, who specialised in fundraising for the unit and only joined full-time as a combatant in February.

In its early days, the unit used commercial surveillance drones, but its team of engineers, software designers and drone enthusiasts later developed their own designs.

They built a range of surveillance drones, as well as large 1.5-metre eight-rotor machines capable of dropping bombs and rocket-propelled anti-tank grenades, and created a system called Delta, a network of sensors along the frontlines that fed into a digital map so commanders could see enemy movements as they happened. It now uses the Starlink satellite system, supplied by Elon Musk, to feed live data to Ukrainian artillery units, allowing them to zero in on Russian targets.

The unit was disbanded in 2019 by the then defence minister, but it was hastily revived in October last year as the Russian invasion threat loomed.
The ability to maintain an aerial view of Russian movements has been critical to the success of Ukraine’s guerrilla-style tactics. But Aerorozvidka’s efforts to expand, and to replace lost equipment, have been hindered by a limited supply of drones and components, and efforts to secure them through defence ministry procurement have produced little, partly because they are a recent addition to the armed forces and still considered outsiders.

Furthermore, some of the advanced modems and thermal-imaging cameras made in the US and Canada are subject to export controls, so they have resorted to crowdfunding and asking a global network of friends and supporters to find them on eBay or other websites.
Marina Borozna, who was an economics student at university with Taras, is exploring ways of buying what the unit needs and finding routes to get the supplies across the border.

“I know there are people who want to help them fight, people who want to do a bit more than the humanitarian aid,” Borozna said. “If you want to address the root cause of this human suffering, you’ve got to defeat the Russian invasion. Aerorozvidka makes a huge difference and they need our support.”

Her partner, Klaus Hentrich, a molecular biologist in Cambridge, is also helping the effort, drawing on his experience as a conscript in the German army.

“I was in an artillery reconnaissance unit myself, so I immediately realised the outsized impact that Aerorozvidka has. They effectively give eyes to their artillery,” Hentrich said. “Where we can make a difference is to rally international support, be it financial contributions, help to get harder-to-find technical components or donations of common civilian drones.”

The unit is also looking at ways to overcome Russian jamming, part of the electronic warfare being waged in Ukraine in parallel to the bombs, shells and missiles. At present, Aerorozvidka typically waits for the Russians turn off their jamming equipment to launch their own drones, and then it sends up its machines at the same time. The unit then concentrates its firepower on the electronic warfare vehicles.

Honchar describes these technological battles, and Aerorozvidka’s way of fighting, as the future of warfare, in which swarms of small teams networked together by mutual trust and advanced communications can overwhelm a bigger and more heavily armed adversary.

“We are like a hive of bees,” he said. “One bee is nothing, but if you are faced with a thousand, it can defeat a big force. We are like bees, but we work at night.”
Meleket wrote:
23 Mar 2022, 11:14
ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ፡ ዲጅታሎቹን ያስመረረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው ኤርትራዊ በትር - ታሪክ ይቀጥላል :mrgreen:
Meleket wrote:
15 Mar 2019, 03:25
1.3 የውጊያው አፈጻጸም ሂደት (17-19 መጋቢት)
....
ናደው እዝ ሲደመሰስ እጅግ ብርቱ ውጊያ የተካሄደት ስፍራ ‘ሞጋዕ ቀጣሪት”ና ‘ቃምጨዋ’ ይባላሉ። የኢትዮጵያ ሰራዊት አዛዦች፡ ከተራራማ ገዢና ስትራቴጂያዊ ስፍራዎች ተገፍቶ ብትንትኑ ወጥቶ ወደ ተጠቀሱት ሰርጦችና ጅረቶች የወረደውን እግረኛ ሰራዊት፡ ዳግም ተደራጅቶ የከባድ መሳርያ መሽጎበት የነበረውን የደጀን ቦታቸውን ሊከላከልላቸው እንደማይችል በመገምገም፡ እዚያ አካባቢ የነበረውን ማንኛውም መሳርያቸው እንዳይማረክባቸው በአፋጣኝ እንዲያፈገፍጉ ወሰኑ። በዚህም መሰረት ከ 70 እስከ 80 የሚሆኑ ታንኮችና ተሽከርካሪዎች፡ በቀትር ወደ አፍዓበት ጉዟቸውን ተያያዙት። ነገር ግን በ15፡30 አካባቢ እነዚህ በርካታ ታንኮችና ተሽከርካሪዎች፡ ‘ዓሽሩም’ የተባለውን ዳገት ተሰልፈው ይወጡ በነበሩበት ወቅት፡ በ‘ሕዳይ’ ወንዝ በኩል አልፈው ሁነኛ ቦታ ላይ ተዘጋጅተው ይጠብቁ በነበሩ የነጻነት ታጋይ ታንከኞች ዒላማ ውስጥ ገቡ። ከነጻነት ታጋዮች 34ኛ ታንከኛ ብርጌድ ታንኮች አንዷም፡ በርቀት በተኮሰችው ጥይቷ፡ ዓሽሩም ጫፍ ላይ ደርሳ የነበረችን አንዲት ቢ.ኤም. 21 ተወንጫፊ ሮኬት የጫነች መኪናን አቃጠለች። ሁለተኛዋ ከታንኳ የተተኮሰው ጥይትም፡ አቀበቱ መሃል የነበረችን አንዲት ታንክ አቃጠለች። በዚህም ምክንያት “ዘርአይ ደረስ” ተብሎ የሚጠራው የኢትዮጵያ ሰራዊት እጅግ የሚመካበት 29ኛው መካናይዝድ ብርጌድ ተሽከርካሪዎችና ታንኮች መፈናፈኛ መንገድ አጥተው ለብርቱ አደጋ ተጋለጡ።

ይህን ያህል ከባድ መሳርያ የጫኑ መኪናዎችና ታንኮች ማፈግፈጊይና መውጫ ቀዳዳው ሲጠፋቸው፣ ውጊያውን ይመራ የነበረው የኢትዮጵያ (ሁ.አ.ሰ.) አዛዥ ሜጀር ጀነራል ውበቱ ጸጋየ፣ ያ ሁሉ የታገተውና ወጥመድ ውስጥ የገባው ከባድ መሳርያና ታንክ በነጻነት ታጋዮች ቁጥጥር ስር እንዳይገባ፡ የውጊያ አውሮፕላኖች እንዲያጋዩት መመሪያ ሰጠ። በዚያን ቀውጢ ሰዓትም፡ የወገኑን ከባድ መሳርያዎችና ታንኮች እንዲያጋይ ትእዛዝ የተሰጠው የውጊያ ጄት አብራሪም፡ “አዬ መንግስት ሲወድቅ” ብሎ ሲናገር በሬዲዮ ሞገድ ተጠለፈ። በርግጥ ያ እጅግ ሰፊ የሆነው ደምሳሽ የማጥቃት እርምጃ የኢትዮጵያ ሰራዊት ላይ ያሳረፈው ግዙፍ ጠባሳ እጅጉኑ ጎልቶ የታየው ‘ዓሽሩም’ በተባለው ዳገት ላይ ነው።

ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ፡ ዲጅታሎቹን ያስመረረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው ኤርትራዊ በትር - ታሪክ ይቀጥላል :mrgreen:
ሲጠቃለል
መለስ = ፑቲን = የማሌ (የማርክስና የሌኒን ግርፍ) ልዑላዊ ሃገሮችን የወረሩ ወፈፌ መሪዎች

የታላቋ ትግራይ ህልም = የታላቋ ኢትዮጵያ ህልም = የታላቋ ሩስያ ህልም

ደደቢት ብቻ ኣይደለም ደደብ፤ ሩስያም(ክሬምሊንም) ጭምር ደደብ ነው!

ዘለንስኪ ጀግና ነው!

ድል ለሰፊው የዩክሬን ህዝብ!
:mrgreen:

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 14 Mar 2025, 09:43

ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡
ሶቭየት-ሕብረትን ያሳፈረ፡
ሕወሓትን ያደናበረ፡
የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ -

‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክን፡ 37ኛ ዓመቱን
ለመዘከር ያህል ነው!

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 15 Mar 2025, 05:29

Meleket wrote:
23 Mar 2022, 11:14
ምስሉ ላይ የሚታዩት በኤርትራዉያን ታጋዮች የተማረኩ የልዕለኃያል ሃገር ነኝ የምትለው የሶቭየት ህብረት የጦር ኣማካሪ መኮንኖች ናቸው። ድንቄም ኣማካሪ! :mrgreen:

ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ፡ ዲጅታሎቹን ያስመረረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው ኤርትራዊ በትር - ታሪክ ይቀጥላል :mrgreen:
Meleket wrote:
15 Mar 2019, 03:25
1.3 የውጊያው አፈጻጸም ሂደት (17-19 መጋቢት)

የህዝባዊ ግንባር ሰራዊት አስቀድሞ በተጠቀሰው አሰላለፍ፡ መጋቢት 17 1988 ማለዳ በአምስቱ ማእዘኖች የማጥቃት እርምጃውን ጀመረ። ምንም እንኳን የኢትዮጵያ (የደርጉ) ሰራዊት በርትቶና ወጥሮ ለመዋጋት ቢሞክርም፡ ቀኑን ሙሉ በቀጠለው ውጊያ፡ የመጀመሪያና ሁለተኛ የመከላከያ ወረዳውን ለቆ ሲያፈገፍግ፡ ከግንባሩ ውጪ ማለትም በተለያዩ ማእዘኖች እንዲያጠቁ ተመድበው የነበሩት የነጻነት ታጋዮች፡ በጠላት ወረዳ ውስጥ ከከረን አፍዓበት የሚወስደውን መንገድ እንዲያጠቁ የተመደቡትም ጭምር ዓላማቸውን በእቅዱ መሰረት አሳኩ። በኢትዮጵያ ሰራዊት ወረዳ ውስጥ እንዲያጠቃ የተመደበው የነጻነት ታጋዮች 52ኛ ክፍለጦር፣ በዚሁ ዕለት ‘መስሓሊት’ በተባለ ስፍራ በመመሸግ፡ ከከረን ወደ ኣፍዓበት ለረዳትነት የተንቀሳቀሰውን የኢትዮጵያ ሰራዊት ሲከላከል ዋለ።

ውጊያው በሚካሄድበት በሁለተኛው ቀን ማለትም መጋቢት 18፡ በአምስቱ ማእዘኖች የጥቃት እርምጃውን ያካሄደው የነጻነት ታጋዮች ኃይል፡ ብርቱ ረሃብ፣ ጥምንና ድካምን ተቆቁሞ፡ የጎደለውን መሳርያና ጥይት ከኢትዮጵያ ሰራዊት እየማረከና እየተጠቀመ፡ በቅጽበት በመገስገስ፡ ሰፊ ቦታዎችን ተቆጣጠረ። የደርጉ ማለትም የኢትዮጵያ ሰራዊትም በዚህ ሃያልና ፋታ የማይሰጥ የማጥቃት እርምጃ አደረጃጀቱ ተዛብቶ፡ አዛዥና ታዛዥ ተደበላልቆ፡ የእዝ ሰንሰለት ተጥሶ፡ አብዛኛው ክፍሉ ቅጥ ባጣ መልኩ ወደኋላ ለመሸሸት ተገደደ።

ናደው እዝ ሲደመሰስ እጅግ ብርቱ ውጊያ የተካሄደት ስፍራ ‘ሞጋዕ ቀጣሪት”ና ‘ቃምጨዋ’ ይባላሉ። የኢትዮጵያ ሰራዊት አዛዦች፡ ከተራራማ ገዢና ስትራቴጂያዊ ስፍራዎች ተገፍቶ ብትንትኑ ወጥቶ ወደ ተጠቀሱት ሰርጦችና ጅረቶች የወረደውን እግረኛ ሰራዊት፡ ዳግም ተደራጅቶ የከባድ መሳርያ መሽጎበት የነበረውን የደጀን ቦታቸውን ሊከላከልላቸው እንደማይችል በመገምገም፡ እዚያ አካባቢ የነበረውን ማንኛውም መሳርያቸው እንዳይማረክባቸው በአፋጣኝ እንዲያፈገፍጉ ወሰኑ። በዚህም መሰረት ከ 70 እስከ 80 የሚሆኑ ታንኮችና ተሽከርካሪዎች፡ በቀትር ወደ አፍዓበት ጉዟቸውን ተያያዙት። ነገር ግን በ15፡30 አካባቢ እነዚህ በርካታ ታንኮችና ተሽከርካሪዎች፡ ‘ዓሽሩም’ የተባለውን ዳገት ተሰልፈው ይወጡ በነበሩበት ወቅት፡ በ‘ሕዳይ’ ወንዝ በኩል አልፈው ሁነኛ ቦታ ላይ ተዘጋጅተው ይጠብቁ በነበሩ የነጻነት ታጋይ ታንከኞች ዒላማ ውስጥ ገቡ። ከነጻነት ታጋዮች 34ኛ ታንከኛ ብርጌድ ታንኮች አንዷም፡ በርቀት በተኮሰችው ጥይቷ፡ ዓሽሩም ጫፍ ላይ ደርሳ የነበረችን አንዲት ቢ.ኤም. 21 ተወንጫፊ ሮኬት የጫነች መኪናን አቃጠለች። ሁለተኛዋ ከታንኳ የተተኮሰው ጥይትም፡ አቀበቱ መሃል የነበረችን አንዲት ታንክ አቃጠለች። በዚህም ምክንያት “ዘርአይ ደረስ” ተብሎ የሚጠራው የኢትዮጵያ ሰራዊት እጅግ የሚመካበት 29ኛው መካናይዝድ ብርጌድ ተሽከርካሪዎችና ታንኮች መፈናፈኛ መንገድ አጥተው ለብርቱ አደጋ ተጋለጡ።

ይህን ያህል ከባድ መሳርያ የጫኑ መኪናዎችና ታንኮች ማፈግፈጊይና መውጫ ቀዳዳው ሲጠፋቸው፣ ውጊያውን ይመራ የነበረው የኢትዮጵያ (ሁ.አ.ሰ.) አዛዥ ሜጀር ጀነራል ውበቱ ጸጋየ፣ ያ ሁሉ የታገተውና ወጥመድ ውስጥ የገባው ከባድ መሳርያና ታንክ በነጻነት ታጋዮች ቁጥጥር ስር እንዳይገባ፡ የውጊያ አውሮፕላኖች እንዲያጋዩት መመሪያ ሰጠ። በዚያን ቀውጢ ሰዓትም፡ የወገኑን ከባድ መሳርያዎችና ታንኮች እንዲያጋይ ትእዛዝ የተሰጠው የውጊያ ጄት አብራሪም፡ “አዬ መንግስት ሲወድቅ” ብሎ ሲናገር በሬዲዮ ሞገድ ተጠለፈ። በርግጥ ያ እጅግ ሰፊ የሆነው ደምሳሽ የማጥቃት እርምጃ የኢትዮጵያ ሰራዊት ላይ ያሳረፈው ግዙፍ ጠባሳ እጅጉኑ ጎልቶ የታየው ‘ዓሽሩም’ በተባለው ዳገት ላይ ነው።

በመጋቢት 18 የውጊያ ውሎም፡ ሲሶው የኢትዮጵያ ሰራዊት ዓቅም ተወቅጦ፡ በግምባር በኩልም ያጠቃ የነበረው የነጻነት ታጋዮች ክፍልም 40 ኪ.ሜ. ወደፊት ገፍቶ፡ የደርጉን ሰራዊት አሉ ከሚባሉት ስትራቴጂያዊ ተረተሮች ጠራርጎ ሲያወርደው፡ በግራና ቀኝ ክንፎች ያጠቁ የነበሩት የነጻነት ታጋዮች ክፍሎች ደግሞ፡ አፍዓበት ከተማ መዳረሻ አካባቢን ተቆጣጥሮ አደረ። ከበስተኋላ ከከረን ወደ አፍዓበት የሚወስደውን መንገድ ግጥም አርጎ ዘግቶት የዋለው የነጻነት ታጋዮች 52ኛ ክፍለጦርም፡ ከከረን ለረዳትነት ይመጣ የነበረን ግዙፍ የደርግ ሰራዊት በብርቱ መስዋእትነት መክቶት ዋለ። ስለሆነም የናደው እዝ በሁሉም አቅጣጫዎች እየተነዳ አፍዓበት አካባቢ እጅግ ጠባብ ቀለበት ውስጥ ለመከበብ ተገደደ።

በሶስተኛው ቀን ማለትም መጋቢት 19 1988 ማለዳ 5፡30 ላይ አፍዓበትን ከቦ ያደረው የነጻነት ኃይሎች ታጋይ ሰራዊት የመጨረሻ የጥቃት እርምጃዎቹን ሰነዘረ። በሁለቱ የማጥቃት ቀናት ከባድ ኪሳራ አጋጥሞት እጅግ የተዳከመው የኢትዮጵያ (ደርጉ) ሰራዊት፣ ለአጭር ጊዜ ተቃውሞ በማድረግ ለመከላከል ቢሞክርም፡ የነጻነት ታጋይ ሃይሎች የጥቃት እርምጃ እጅግ ከባድ ስለነበረ፡ የደርጉ ሰራዊት ንብረቱን እያቃጠለ መሸሸት ጀመረ። በከተማዋ ምስራቅና ደቡባዊ ምስራቅ አቅጣጫ ተጠግቶ ያደረው የነጻነት ሃይሎች ተዋጊ ሰራዊትም ማለዳ 9:00 (3፡00) አፍዓበት ከተማ ገስግሶ ገባ። በሰሜንና በሰሜናዊ ምዕራብ ሲገሰግስ ያደረው የነጻነት ታጋዮች ተዋጊ ኃይልም፡ ከረፋዱ 10፡00 (4፡00) ተልእኾውን ፈጽሞ አፍዓበት ከተማ በድል ገባ።

አፍዓበትን ለመቆጣጠር ማለዳ ‘ሻባይ መንደር’ በተባለው ስፍራ በተካሄደው አጭርና ብርቱ ውጊያም፡ የ61ኛው ክፍለጦር 87ኛ ብርጌድ 3ኛ ሻምበል፡ 3 የሶብየት ሕብረት ከፍተኛ የጦር አማካሪዎችንና ሌሎች ኢትዮጵያዉያን መኮንኖችንን ማረከች።

ከዚህ በኋላም በአፍዓበትና በአካባቢዋ በተደረገ ውጊያ ከሞትና ከመማረክ አምልጦ፡ ጥቂት ታንኮቹንና ተሽከርካሪዎችን ይዞ ወደ ከረን ለማምረጥ የሞከረ የኢትዮጵያ ሰራዊት፡ የነጻነት ታጋዮች 52ኛው ክፍለጦር አዘጋጅቶት በቆየ ወጥመድ ውስጥ ስለገባ፡ ንብረቱን ጥሎ እግሬ አውጪኝ ብሎ በ ‘ግዝግዛ’ ‘ቀልሃመትና’ ‘ሂካኖ’ በተባሉት ስፍራዎች ብትንትኑ ወጣ።

የናደውን እዝ የመደምሰስ ብርቱ ውጊያም፡ መጋቢት 19 1988 ከቀትር በኋላ ‘ግዝግዛ’ በተባለው ስፍራ በተካሄደ የመጨረሻ ውጊያም ተደመደመ። ከውጊያው በፊት ከነጻነት ታጋይ የሰራዊት አዛዦች አንዱ እንደተነበየውም፡ ደርጉ እጅግ ይመካበት የነበረው ብርቱ የሰራዊቱ ክፍል የሆነው “ናድው እዝ” የቀብር ስነስርዓቱ በኤርትራዉያን ታጋዮች ድል ተፈጸመ

የኤርትራ የነጻነት ታጋዮች፡ አስር ዓመታት ያህል ያለመታከት በናቅፋ ግንባር ያደርጉትን የመመከት ተልዕኾ አገባደው፡ ‘መስሓሊት’ በተባለው ስፍራ አካባቢ “ የከረን ግንባር” የሚባል አዲስ ግንባር በመክፈት፡ ወደ አዲስ የማጥቃት ስትራቴጂካዊ መድረክ የሚያሸጋግር የበላይነቱን ጨበጡ።

በቀጣይ ናድው እዝን የመደምሰሱ ተልእኾ በኢትዮጵያ ሰራዊት ላይ ያሳደረው ተጽእኖና የዚህን ጦርነት ልዩ ገጽታ እናያለን።


ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ፡ ዲጅታሎቹን ያስመረረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው ኤርትራዊ በትር - ታሪክ ይቀጥላል :mrgreen:
Meleket wrote:
14 Mar 2025, 09:43
ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡
ሶቭየት-ሕብረትን ያሳፈረ፡
ሕወሓትን ያደናበረ፡
የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ -

‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው ኤርትራዊ በትር - ታሪክን፡ 37ኛ ዓመቱን
ለመዘከር ያህል ነው!

Meleket
Member
Posts: 4364
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ - ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ

Post by Meleket » 20 Mar 2025, 09:40

Meleket wrote:
18 Mar 2019, 09:49
የናደው እዝን የደመሰሰው የማጥቃ እርምጃ አስተዋጽኦና ብርቅነቱ

የናደው እዝን ለመደምሰስ የተካሄደው የማጥቃት እርምጃ፣ በኤርትራ ህዝብ የነጻነት ትግል ታሪክ ውስጥ በዓይነቱም ሆኑ በውጤቱ እጅግ ልዩ ደማቅና አንጸባራቂ ወታደራዊ የድል ታሪክ ነው። ይህን ድል ልዩና ብርቅ የሚያደርጉ ምክንያቶችም፡ አንድ እጅግ ግዙፍ የሆነን ጨቋኝ ሰራዊትን ሙሉ በሙሉ ከበባ ውስጥ በማስገባት ለወሬ ነጋሪ እንኳን ሳታስቀር ሙሉ በሙሉ የመደምሰስ ሂደት በመከናወኑ ነው። ከዚህ የማጥቃት እርምጃ በፊት የነበረው መድረክ፡ የነጻነት ታጋዮች በኢትዮጵያ ሰራዊት ላይ ብዙ ግዙፍና ጥቃቅን ጥቃቶችን ያካሂድ የነበረ ቢሆንም እንኳን፡ ሁሉም እነዚህ የማጥቃት እርምጃዎች፡ ጠላትን በመገፍተርና በመግፋት ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ለመቆጣጠር ያተኮሩ ነበሩ እንጂ እንደዚህኛው የጥቃት እርምጃ ጠላትን ቀለበት ውስጥ በመክበብ ሙሉ በሙሉ ለመደምሰስ ያለሙ አልነበሩም።

የነጻነት ታጋዮች ሃይል ከ1978 አጋማሽ ጀምሮ ለአስር አመታት የተካሄደን ረዢም የህልውና ውጊያ፡ ከጠላት በርካታ መሳሪያዎችና ታንኮችን በመማረክ የተኩስ ብቃቱን ለማጎልበት በቅቷል። ናደው እዝን በመደምሰሱም፡ የተኩስ አቅሙን ይበልጥ የሚያጎለብቱ፡ ከዚያ በፊት ማርኮ የማያቃቸውን የ130 ሚ.ሜ. መድፍና ቢ.ኤም 21 ተወንጫፊ ሮኬት ሚካይሎችን ሲማርክ፡ ከ50 በላይ ታንኮች የሚገኙባቸው በርካታ መሳሪያዎችንና ጥይቶችን ለመማረክ ችሏል። ከዚህም በተጨማሪ፡ የናድወ እዝን በመደምሰስ ሂደት፡ የነጻነት ታጋዮች ለመጀመሪያ ግዜ ሶስት የሶቭየት ህብረት ዜጋ የሆኑ የጦርነት አማካሪዎችን ለመማረክ ችለዋል።

ይህ ግዙፍና ቅጽበታዊ የማጥቃት እርምጃ በደርጉ ስርዓት ውስጥ ከፍተኛ ነውጥንና ሽብርን ፈጥሯል። በመሆኑም ከጥቃቱ ማግስት ማለትም መጋቢት 31 1988 በተካሄደ አስቸኳይ የኢ.ሰ.ፓ ማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ወቅት፡ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅና የክተት አዋጅ ለማውጣት ተገዷል። መንግስቱ ኃይለማርያም በስብሰባው ባሰማው ንግግርም፡ የኢትዮጵያ ህልውና ስጋት ውስጥ መውደቁን በመግለጽ፡ “ጥያቄው ወንበዴዎች ይጥፉ ወይስ እኛ እንጥፋ ነው?” በማለት ደንፍቷል። በዚያ ወቅት በወጣው የክተት አዋጅም፡ በተለያየ ምክንያት ከሰራዊት ተሰናብተው የነበሩ የሰራዊቱ መደበኛ አባላት እንዲሁም የብሄራዊ ውትድርና አገልግሎት አባላት፡ ወደ ሰራዊቱ እንዲመለሱ ሲደረግ፡ ስልጠና ላይ የነበሩት 5ኛ ዙር የብሄራዊ አገልግሎት ወታደሮች በአጭር ግዜ ስልጠናቸውን አገባደው ቅድመ ግንባር ውስጥ እንዲገቡ ተደርጓል።

የደርጉ መሪ መንግስቱ ኃይለማርያምም በዚያን ሰሞን ከሶማሊያው መሪ ከሲያድ ባረ ጋር በጥድፊያ የሰላም ስምምነት እንዲፈርም ያስገደደውም ይህ የናደው እዝ በመደምሰሱ የተገኘ ፍሬ ነው። ያኔዉኑም በምስራቅ ከነበረው ሰራዊቱ ግዙፍ ክፍሉን ወደ ኤርትራ አጓጉዟል። በትግራይና በምእራብ ኢትዮጵያ የነበሩትን የ3ኛ 9ኛና 10ኛ ክፍለጦሮችንም ወደ ኤርትራ በጥድፊያ አጓጉዟል። ደርጉ ትግራይ ውስጥ ለጥበቃነት ያቆየው የሰራዊት ዓቅሙ በጥቂት ከተሞች ብቻ በመወሰኑ፡ ብዙው የትግራይ ክፍል በቀላሉ ከደርጉ ቁጥጥር ውጭ ሆነ። (ትግራይ ነጻ የምትወጣው ኤርትራ ውስጥ በተካሄደ ውጊያ ወላፈን አማካኝነት ነው ማለት ነው።) በቅጽበት ደርግ ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ወደ ኤርትራ ያጋዘው የሰራዊት ብዛት ከ90,000 በላይ ሆኖ ነበር።

ከዚህ በተጨማሪም ደርጉ፡ በምዕራብ ኤርትራ ከከረን እስከ ተሰነይ አሰልፎት የነበረው “በርግድ እዝ’ የተባለው ሰራዊቱ በቅጽበት እንዲያፈገፍግ ተገዷል። በምስራቅም የነጻነት ታጋዮች ሳህልን ከሰሜናዊ ባሕሪና የሰምሃር ሜዳዎች ጋር የሚያገናኘውን ሰፊ ቦታ ለመቆጣጠር ችለዋል። እነዚህን ቦታዎች መቆጣጠራቸውም በቀጣይነት “ፈንቅል” የተባለውን ልዩ ጥቃትና ብርቅ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ያስገኘን ጥቃት ለመሰንዘር በር ከፍቷል።

ናደው እዝን ከደመሰሰ በኋላ የነጻነት ታጋዮች ኃይል የጨበጠውን ድል ለማስጠበቅና ይበልጥም ለማስፋት ይችል ዘንድ፡ በሓልሓል ግንባር ላይ መሽጎ በነበረው “መንጥር እዝ’ ላይ ከፍተኛ አይምሬ ጥቃትን በመሰንዘር ከባድ ኪሳራ በደርጉ ላይ አድርሶ ሰፊ ቦታዎችን ሲቆጣጠር፣ በከረን አካባቢም ተደጋጋሚ የማጥቃት እርምጃዎች በመሰንዘር፡ አዲሱን የመከላከያ ወረዳውን ለማደላደል ችሏል። የደርጉም የነጻነት ታጋዮች የተጎናጸፉትን ድል ለመቀልበስ ከየቦታው አሰባስቦ ባመጣውን ግዙፍ ሰራዊት አድርጎ በአዲሱ የከረን ግንባር በኩል ሰፊ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ ወሰደ። በሮራ መንሳዕና እንሲ፡ በግልንዲ፣ ግዝግዛ፣ ዓጋመትና እንዲሁም በዓንሰባ ወንዝና ሓልሓል በኩልም ለወራት የዘለቀ ብርቱ ውጊያ ተካሄደ። ደርጉ በግንባር በኩል ያካሂደው ከነበረው ውጊያ በተጨማሪ የ102ኛ አየር ወለድ ሰራዊቱን በስውር አንቀሳቅሶ፡ በምስራቃዊው ሜዳማ ቦታዎች በኩል ተዟዙሮ ወደ አፍዓበት የመግባት ያለመ የከሸፈ ጥቃትን ሰንዝሮ ነበር። በዚህ ያልተጠናና የጥድፊያ የጥቃት እርምጃ፣ ክፍለጦሩ በሙሉ ገና ጥቃት እንኳን ሳይሰነዝር፡ በውሃ ጥምና በረዢም ጉዞ ተሸንፎ፡ ምንም ፍሬ ሳያፈራ ለሞትና ለምርኾኛነት ተዳርጓል።

በወታደራዊ ስትራቴጂ አኳያ ናደው እዝን የመደምሰሱ ሂደትና ተጽዕኖው ሊገለጽ የሚችለው፡ ቀጥሎ ከተካሂዱት የማጥቃት እርምጃዎችና የመልሶ ማጥቃት ውጊያዎች ጋር በሰፊ ዓውድ ነው። በዚህ ለወራት በቆየ የደርጉ የማጥቃትና የመልሶ ማጥቃት ውጊያ ወቅት፡ ደርጉ የከሰረው የሰው ኃይልና ዓቅም፡ ናደው እዝን በመደምሰስ ሂደት ከከሰረው ቢበዛ እንጂ አያንስም። በነዚህ ውጊያዎች የነጻነት ታጋዮች ናደው እዝን በመደምሰስ ሂደት የተቆጣጠሯቸውን ሰፊ ቦታዎች ለማቀብ መቻላቸው፡ ደርጉም ብዙ የማጥቃት እርምጃዎችን ቢሰነዝርም ፋይዳቢስ ሆኖ በመቅረቱ፡ ወታደራዊው ሚዛን ሙሉ በሙሉ ወደ ኤርትራዉያን ታጋዮች ማጋደሉን አጉልቶ የሚያሳይ ነው። ናደው እዝን ለመደምሰስ የተሰነዘረው ብርቱ በትር መላዋን ኢትዮጵያን የናጠ፡ (ወያኖችንም በፍራት አንቀጥቅጠው እንደነበሩ ተራኪው አልገለጸውም፡ እኛም ይሁና ብለን ታዝበነዋል) ተጽዕኖው እስከ ሞቃዲሾና የሶቭየት ህብረት ቤተመንግስት ክሬምሊን ድረስ የደረሰ ነበር። ይህም ሲባል ከናደው እዝ መደምሰስ በኋላ ሶስት ከፍተኛ መኮንኖቿ በውጊያው የተማረኩባት ሶቭየት ህብረትም ብትሆን፡ ደርጉ እንደማያሸነፍ ገምግማለች። ልክ በዚያ የታሪክ መድረክም በሶቭየት ህብረት ውስጥ የመጣው የፖሊሲ ለውጥ ወይም ተሃድሶው ተጨምሮበት የክሬምሊን ሰዎች ከደርጉ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት አቀዝቅዘውት ነበር።

ናደው እዝን የመደምሰስ ውጊያ፡ ደርጉ የኤርትራዉያን ታጋዮችን እንቅስቃሴ ለመግታት የነበረውን ህልም ሙሉ በሙሉ ያበነነ፡ የኤርትራ ነጻነት በፍጹም አይቀሬ መሆኑን ለዓለም ግልጽ ያደረገ ድል ነው። ስለሆነም ከናደው እዝ መደምሰስ በኋላ የኤርትራ ጉዳይ በዓለም የዜና መድረክ ውስጥ ትልቅ ትኩረት አግኝቶ ነበር። ታዋቂው የታሪክ ተመራማሪና ጸሓፊው እንግሊዛዊው በዚል ደቪድሰን የጦርነቱን ውጤት በዓይኑ ከታዘበ በኋላ “ከድየን ብየን ፉ በኋላ፡ በአንድ የነጻነት እንቅስቃሴ የተከናወነ ግዙፍ ወታደራዊ ኦፕሬሽን” በማለት የኤርትራዉያን ታጋዮችን ድል ገልጾታል። የድየን ብየን ፉና ናደው እዝን የመደምሰስ ውጊያዎች በተጽዕኗቸው ማለትም የገዢዎችን ዕድሜ በማሳጠር ረገድ ተመሳሳይ ቢሆኑም እንኳን፡ እንደ ወታደራዊ ክንውን ግን ናደው እዝን የመደምሰስ ሂደት ከድየን ብየን ፉ’ዉ እጅግ የላቀና የገዘፈ ነው። ከዚህ የኤርትራዉያን ድል በኋላ በርካታ ሃገሮች የኤርትራ ጉዳይ ሰላማዊ መፍትሄ እንዲያገኝ ጥሪ አድርገዋል። ደርጉም አስቀድሞ አሻፈረኝ ሲል እንዳልነበረ የሰላም ውይይትን ለማድረግ ተገዷል።

ምንም እንኳን የታሪኩ ጸሃፊ ( ታጋይ ሰለሙን በርሀ) ከዚህ ብርቅ የኤርትራዉያን ታጋዮች ድል አንጻር የሕወሃትን መደናበር በቅጡ ባያቀርበውም ላደረገው ታሪክን በበኩሉ የመመዝገብ እርምጃ ምስጋናችንን እናቀርብለታለን።

ይህን በመሰለ የበርካታ ዓመታት ውጊያ ነጻ የወጣችን ልዑላዊት ሃገር በመደመር ይሁን በማባዛት ስሌት ‘አፈፍ’ ለማድረግ የምትቋምጡ ጅሎች ካላችሁ ደግሞ ህልም ወይም የቀን ቕዥት መሆኑን ለመግለጽም እንወዳለን። ህወሃቶችም የኤርትራን ህዝብ የተባበረ ጡንቻና የኤርትራ ህዝብን ትዕግስት በደንብ አድርጋችሁ ታውቁታላችሁ አግአዚ ይሁን ትግራይ ትግርኝ ይሁን ሌላ ፍልስፍና ኤርትራዉያንን አያወናብድም፡ ይልቅ ካርታችሁን አሻሽላችሁ መሬታችሁ ያልሆነን መሬት ለባለቤቱ ለኤርትራ ህዝብ በሰላም አስረክባችሁ በንስሃና በፍቅር ኑሩ ለማለት ነው። በሚገባችሁ ቋንቋ ግልጽ ለማድረግ
“ናይና አይንህብይ ላይ እንዳማትና'ለ ኣይንደልይ!!!”


ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡ ሶቭየትሕብረትን ያሳፈረ፡ ሕወሓትን ያደናበረ፡ ዲጅታሎቹን ያስመረረ- ‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው በትር - ታሪክ ዘላለም ይኖራል እየተነገረ!!!
ከዚህ ታሪክ ምን እንማራለን ከተባለ፡ አንድ ነጻነቴን ያለ ህዝብ የተለያዩ ኃይሎች ተቀናጅተው ሊደመስሱት ቢሞክሩም እንኳ፡ በጽናት ከታገለ ማንኛውንም ኃይል ማሸነፍ እንደሚችል ነው። ኤርትራውያን በሶቭየት ህብረት አጋርነትና አማካሪነት እስከ አፍንጫው የታጠቀውን የደርግ ሰራዊት በቅጽበት በመደምሰስ፡ የሶቭየት ኅብረት የጦር አማካሪዎችን ሳይቀር ለመማረክ የበቃነው፡ የነጻነት ትግላችን ፍትሓዊና ቅኑ ስለነበረ እኛም ቁርጠኝነት ስላሳየን ብቻ ነው። አሁንም ልዑላዊት የሆነችውን ሃገረ ዩክሬን በመውረር፡ "ታላቂቱን ሩሲያ ዳግም የመመስረት የቀን ቅዥት" ወፈፌውን ፕረዚደንት ፑቲን ስለተጠናወተው፡ በከባድ መሳርያ እውርድንብሱን በመደብደብ "ታላቂቱ ሩሲያ" የምትመሰረት ቢመስለውም እንኳ፡ ፍትሓዊው የዩክሬን ህዝብ ትግል ፍሬ አፍርቶ፡ እንደ ኤርትራ ህዝብ ሶቭየቶችን አሳፍሮ በሰላም የሚኖርበት ግዜ ሩቅ እንዳልሆነ ነው።

"የታላቂቱ ትግራይ ህልም" = "የታላቂቱ ኢትዮጵያ ህልም" = "የታላቂቱ ሩስያ ህልም" ሁሉም ተመሳሳይ የመስፋፋትና ግዛትን የማስፋፋት ህልሞች፡ በህዝቦች ይሁኝታ ካላገኙ፡ የቀን ቅዠት እንደሆኑ፡ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች በኤርትራዊ ጭዋነትና ኩራት ለጠላትም ለወዳጅም ግልጽ ማድረግ ታሪካዊ ኃላፊነታችንን መወጣት ማለት ነው። :lol:

የከርሞ ሰው ይብለንና፡ ራሻ ልኳን አውቃ፡ የዩክሬን ህዝብም በገዛ ሃገሩ ያሻውን የሚያደርግበት ዘመን እንደሚመጣ በልበ ሙሉነት በመግለጥ፡ የጦር ጥቅመኞችንና የወራሪ ደጋፊዎችን በመጠየፍ ጽሑፋችንን ደመደምን፡ እኛ ኤርትራዉያን የመሃልና የመስመር ዳኞች።
:mrgreen:
Meleket wrote:
14 Mar 2025, 09:43
ደርግን በኣፍዓበት ያሳረረ፡
ሶቭየት-ሕብረትን ያሳፈረ፡
ሕወሓትን ያደናበረ፡
የጦር ጥቅመኞችን ያንጨረጨረ -

‘ናደው እዝ’ ላይ ያረፈው ኤርትራዊው በትር - ታሪክን፡ 37ኛ ዓመቱን
ለመዘከር ያህል ነው!

Post Reply