Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 42903
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

በኢትዮጵያ የሰፈነው የጎሳ ፖለቲካ ስርዓትና የወጣቱ ትምህርትና እውቀት ዝቅጠት! የማይቀረው የትምህርት አብዮት! #No More Ethnocratic Authoritarianism!

Post by Horus » 22 Mar 2022, 01:34

በ30 አመት ውስጥ ለመጀምሪያ የኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓትና ጥራት እንደ አቢይ ያገሪቱ የፖለቲካ ውዝግብ ሆኖ እየተነሳ ነው ። ይህ እጅግ እጅግ አስፈላጊና ከማንኛውም ሌላ የፖለቲካ ጥያቄ ተነስቶ ትግል እንዲደረግበት የሚያስፈልግ ጉዳይ ነው።

የጎሳ ስርዓትን ከስሩ ነቅሎ ከሚጥለው ግዙፍ ሃይል ምናልባትም አንደኛና ብቸኛው ትህምህርትን ከዘር ፖለቲካ ነጥሎ መልሶ ሃላፊነቱን ለወላጆች፣ ለመምህራንና ለትምህርት አሰዳደር ሊቃውንት ባለሙያ ስልታሞች መስጫው ዘመን ነው ።

አሁን የሰሞኑ ውዝግብና ትግል 12ኛ መልቀቂያ ማትሪክ ሊሆን ይችላል። ነገ ሌላ የካሪኩለም ትግል አለ ። ከዚያም የትምህርት ጥራትና ብቁና ብቁ ያልሆኑ ተማሪዎች ማጣሪያ ሲስትም ይሆናል ።

ቀጥሎ በየኮሌጁ በየሰሚስተሩ እየወደቀ የሚሰናበተው እጅግ ብዙ ተማሪ አለ ። ከዚህ በኋላ በኮታ ገብቶ በኮታ የዉሸት ዲፕሎማና ድንቁርና ይዞ መመረቅ ቀርቷል! መቅረትም አለበት!

ሌላው ከዚህ በታች እንዳለው አዲስ ተግባራዊ የሚሆነ የአንደኛ ዲግሪ መልቀቂያ አገር አቀፍ እስታንዳርድ የየትምሀር መስኩ መልቀቂያ ፈተና መተግበሩ ነው ። ይህም ማለት አንድ የባዮሎጂ ሜጀር ባችለር ተመራቂ ማወቅ ያለበት አገር አቀፍ ዩኒቨርሳል የእውቀትና ክህሎት መለኪያ ፈተና ይኖራል ማለት ነው።

ብቻ በዚህም በሉት በዚያ የኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ስር ነቀል አብዮት እንደ ሚካሄድበት ጥርጥር የለውም ።

Last edited by Horus on 22 Mar 2022, 12:01, edited 2 times in total.

kibramlak
Member
Posts: 2155
Joined: 26 Sep 2013, 09:27

Re: በኢትዮጵያ የሰፈነው የጎሳ ፖለቲካ ስርዓትና የወጣቱ ትምህርትና እውቀት ዝቅጠት! የማይቀረው የትምህርት አብዮት!

Post by kibramlak » 22 Mar 2022, 07:14

ማህበረሰቡ በማይልቋርጥ የንሮ ውድነት በሚያንገሸግሽ መልኩ እየተናጠ ነው

ፍትህ የሚባር በሀገሪቱ ጠፍቶ በጎሳ ፍርደ ገምድል ተተክቷል

የማህበረሰቡን ደህነት በተመለከተ ብዙ ተብሏል: የሰው በእሳት መቃጠል እንኳን ለጎሳ ፅንፈኞች ምንም ደንታ አልሰጣቸውም

እና ለእነዚህ ችግሮች መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ ብፕየጊዜው አጀንዳ ይፈጠራል፣

- ወንጀለኞችን መፍታት
- መስቀል አደባባይ
- አድዋ
- ዘይት
- ማትሪክ ውጤት
- ......

Abere
Senior Member
Posts: 15495
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: በኢትዮጵያ የሰፈነው የጎሳ ፖለቲካ ስርዓትና የወጣቱ ትምህርትና እውቀት ዝቅጠት! የማይቀረው የትምህርት አብዮት!

Post by Abere » 22 Mar 2022, 09:01

የአብዮት ማዕበል ጎርፍ መጥቶ ሙሉ በሙሉ እንደሚጠራርገው እርግጠኛ ሁኜ መናገር እችላለሁ። የተፈጥሮ ማህበራዊ ዑደት ህግጋት ነው - ከሰው ህሌና በላይ ነው - ኦነግ ሰማይ ቢወጣ፤ወያኔ ምድር ቢወርድ፤ ተረኛ ውታፍ ነቃዮች የምክንያት ውርጅብኝ ቢያዥጎደጉዱ፤ ለዐብይ አህመድ ቅኔ መወድስ ደርድረው ቢያጨበጭቡ - ስር-ነቀል ለውጥ ይመጣል። በግለሰቦች ወይም በቡድኖች በጎአድራጊነት አይደለም። ሊያልፍ ቀን አስተዛዘበን ግን በርካታ ኦሮሙማዎች ከሰው ባህርይ ወጥተው እራሳቸውን አዋርደው እንሰሳ መንጋ መሆናቸውን በአይናችን አየን።

ቀዳማዊው አብዮት ከመሬት ከበርቴ ፊውዳል ሲሆን ይህኛው አብዮት ግን እጅግ ወደ ኋላ ቀርነት በሆነው የጎሳ ወይም የባርባሪዝም(Barbarism) ስርዐት ላይ ነው።



አብዮት! አብዮት! አብዮት! - መሰረታዊ ገፊ ምክንያቶቹ ሙሉ በሙሉ ተሟልተዋል። ይህኛው ዐብዮት መልካም ገድ ያለው ያድርገው።

kibramlak
Member
Posts: 2155
Joined: 26 Sep 2013, 09:27

Re: በኢትዮጵያ የሰፈነው የጎሳ ፖለቲካ ስርዓትና የወጣቱ ትምህርትና እውቀት ዝቅጠት! የማይቀረው የትምህርት አብዮት!

Post by kibramlak » 22 Mar 2022, 09:28

ሊከሰት የሚችለው አብዮት በመጀመሪያ ደረጃ የ"ክልል" ተወካይ ሌቦችን ቀድሞ መግለብ ይገባዋል፣ በዋንኝነት የአማራን ህዝብ እንወክላለን ብለው በህዝብ ደም እና ስቃይ እራሳቸውን እያበለፀጉ ያሉ እንደመሆናቸው ለማንም ማህበረሰብ የማይጠቅሙ ናቸው፣፣ የጠቅላይ ሴረኛው የሴራ ተባባሪዎችም ስለሆኑ፣፣
Abere wrote:
22 Mar 2022, 09:01
የአብዮት ማዕበል ጎርፍ መጥቶ ሙሉ በሙሉ እንደሚጠራርገው እርግጠኛ ሁኜ መናገር እችላለሁ። የተፈጥሮ ማህበራዊ ዑደት ህግጋት ነው - ከሰው ህሌና በላይ ነው - ኦነግ ሰማይ ቢወጣ፤ወያኔ ምድር ቢወርድ፤ ተረኛ ውታፍ ነቃዮች የምክንያት ውርጅብኝ ቢያዥጎደጉዱ፤ ለዐብይ አህመድ ቅኔ መወድስ ደርድረው ቢያጨበጭቡ - ስር-ነቀል ለውጥ ይመጣል። በግለሰቦች ወይም በቡድኖች በጎአድራጊነት አይደለም። ሊያልፍ ቀን አስተዛዘበን ግን በርካታ ኦሮሙማዎች ከሰው ባህርይ ወጥተው እራሳቸውን አዋርደው እንሰሳ መንጋ መሆናቸውን በአይናችን አየን።

ቀዳማዊው አብዮት ከመሬት ከበርቴ ፊውዳል ሲሆን ይህኛው አብዮት ግን እጅግ ወደ ኋላ ቀርነት በሆነው የጎሳ ወይም የባርባሪዝም(Barbarism) ስርዐት ላይ ነው።



አብዮት! አብዮት! አብዮት! - መሰረታዊ ገፊ ምክንያቶቹ ሙሉ በሙሉ ተሟልተዋል። ይህኛው ዐብዮት መልካም ገድ ያለው ያድርገው።

Abere
Senior Member
Posts: 15495
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: በኢትዮጵያ የሰፈነው የጎሳ ፖለቲካ ስርዓትና የወጣቱ ትምህርትና እውቀት ዝቅጠት! የማይቀረው የትምህርት አብዮት!

Post by Abere » 22 Mar 2022, 10:02

አብዮት ሰደድ እሳት ነው ይባላል እኮ። እነማን እሳቱ የሚበላቸው ማገዶዎች እንደ ሆኑ ያውቃቸዋል። ዋና ወያኔ እና ኦነግ እኮ ያለው አማራ ውስጥ ነው። በወያኔ ጊዜ ከመቀሌ ይበልጥ አክራሪ ወያኔ የነበረባት ባህርዳር ነበረች። አሁንም ከነቀምቴ ይበልጥ ኦነግ ያለው ባህር ዳር ነው። የአብዮቱ መጀመሪያ ሰለባዎች የሚገኙት አማራ ክልል ውስጥ ነው።
kibramlak wrote:
22 Mar 2022, 09:28
ሊከሰት የሚችለው አብዮት በመጀመሪያ ደረጃ የ"ክልል" ተወካይ ሌቦችን ቀድሞ መግለብ ይገባዋል፣ በዋንኝነት የአማራን ህዝብ እንወክላለን ብለው በህዝብ ደም እና ስቃይ እራሳቸውን እያበለፀጉ ያሉ እንደመሆናቸው ለማንም ማህበረሰብ የማይጠቅሙ ናቸው፣፣ የጠቅላይ ሴረኛው የሴራ ተባባሪዎችም ስለሆኑ፣፣
Abere wrote:
22 Mar 2022, 09:01
የአብዮት ማዕበል ጎርፍ መጥቶ ሙሉ በሙሉ እንደሚጠራርገው እርግጠኛ ሁኜ መናገር እችላለሁ። የተፈጥሮ ማህበራዊ ዑደት ህግጋት ነው - ከሰው ህሌና በላይ ነው - ኦነግ ሰማይ ቢወጣ፤ወያኔ ምድር ቢወርድ፤ ተረኛ ውታፍ ነቃዮች የምክንያት ውርጅብኝ ቢያዥጎደጉዱ፤ ለዐብይ አህመድ ቅኔ መወድስ ደርድረው ቢያጨበጭቡ - ስር-ነቀል ለውጥ ይመጣል። በግለሰቦች ወይም በቡድኖች በጎአድራጊነት አይደለም። ሊያልፍ ቀን አስተዛዘበን ግን በርካታ ኦሮሙማዎች ከሰው ባህርይ ወጥተው እራሳቸውን አዋርደው እንሰሳ መንጋ መሆናቸውን በአይናችን አየን።

ቀዳማዊው አብዮት ከመሬት ከበርቴ ፊውዳል ሲሆን ይህኛው አብዮት ግን እጅግ ወደ ኋላ ቀርነት በሆነው የጎሳ ወይም የባርባሪዝም(Barbarism) ስርዐት ላይ ነው።



አብዮት! አብዮት! አብዮት! - መሰረታዊ ገፊ ምክንያቶቹ ሙሉ በሙሉ ተሟልተዋል። ይህኛው ዐብዮት መልካም ገድ ያለው ያድርገው።

Horus
Senior Member+
Posts: 42903
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: በኢትዮጵያ የሰፈነው የጎሳ ፖለቲካ ስርዓትና የወጣቱ ትምህርትና እውቀት ዝቅጠት! የማይቀረው የትምህርት አብዮት!

Post by Horus » 22 Mar 2022, 11:55

ለነዚህ ሁሉ ሊፈነዱ ለደረሱ ችግሮች መፍትሄ የመጀመሪያ ወጅግ ወሳኙ እርምጃ የወያኔ ሕገ መንግስት ለእርማትና ለውጥ ባስቸኳይ ለሕዝብ ክርክርና ሃሳብ ሙሉ በሙሉ በግልጽ በሚዲያ ጭምር ዛሬውኑ መጀመር ነው ።

ብልጽግና ተብዬው አዲስ እብሪተኛ የጎሳ ከበርቴዎች ጥርቃሞ በዉሸት ኢትዮጵያዊነት የአንድ ፓርቲ አምባገነን የሌቦች መንግስት ሌላ ልክ እንደ ትግሬ ሌቦች ለ30 አመት በአገሪቱ ላይ ልጭን እየዳዳው ነው። ትግሬ ያቆመው የጎሳ አምባ ገነነት መንግስት (ኤትኖክራቲች አውቶሪታሪያንዝም፣ Ethnocratic Authoritarianism) ባስቸኳይ ባስችኩዋይ መፍረስ ይኖርበታል ። ያ ካልሆነ አይደለም የትምህርት አብዮት የፖለቲካ አብዮት አይቀሬ ነው ።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ሌላ 27 አመት የጎሳ አምባገነን ስርዓት የሚሸከምብት ትከሻ የለውም!

Post Reply