Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

Ethiopia Sheger Dabo ሸገር ዳቦ: The price of government subsidized & retailed bread for the poor has increased by 91%

Post by sarcasm » 10 Mar 2022, 21:47

ሸገር ዳቦ ዋጋውን በእጥፍ አሳድጎ ወደ ሥራ ተመለሰ
9 March 2022
አማኑኤል ይልቃል


ባጋጠመው የግብዓት ዋጋ መወደድ ምክንያት ከአንድ ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ አቅርቦቱን አቋርጦ የቆየው ሸገር ዳቦ፣ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ወደ ሥራ መመለሱ ተገለጸ፡፡ በ900 ሚሊዮን ብር ወጪ ተገንብቶ ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት ሥራ የጀመረው ሸገር ዳቦ፣ በአንድ ብር ከ20 ሳንቲም ሲሸጥ የነበረውን ዳቦ በሁለት ብር ከአሥር ሳንቲም እንዲሸጥ መወሰኑን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል፡፡

በ2012 ዓ.ም. ፋብሪካው ሲመረቅ በሰዓት 80 ሺሕ ዳቦ በማምረት በሦስት ፈረቃ እስከ ሁለት ሚሊዮን ዳቦ እንደሚያቀርብ ተነግሮ የነበረ ቢሆንም፣ ፋብሪካው በቀን ከ700 እስከ 800 ሺሕ ዳቦ ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር አንስቶም በቀን የሚያመርተው የዳቦ መጠን ወደ 1.5 ሚሊዮን ማደጉ መገለጹ ይታወቃል፡፡

ይሁንና ለዳቦ ማከፋፈያነት በተሰጡት 400 ያህል አገልግሎታቸውን የጨረሱ አንበሳ አውቶብሶች አማካይነት በሚቀርበው ዳቦና በነዋሪዎች መካከል ባለው የፍላጎት መጠን መካከል ከፍተኛ ልዩነት አለ፡፡ ፋብሪካው ሥራ በጀመረ በአምስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለ70 ሚሊዮን ብር ኪሳራ መዳረጉን አስታውቆ ነበር፡፡

ፋብሪካው ከአንድ ወር በፊት ሥራ ሲያቆም የግብዓት እጥረትና የዋጋ መወደድ እንዳጋጠመው ያስታወቀ ሲሆን፣ የዋጋ ጭማሪ ለማድረግም ለከተማ አስተዳደሩ ጥያቄ አቅርቦ ነበር፡፡

Dr Abiy's flagship project has increased the price of bread for the poor by 91%


Continue reading https://www.ethiopianreporter.com/index ... icle/24905