የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት አገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የማዋቀሩ ሂደት እንዲቆም ጠየቀ (BBC)
Posted: 14 Feb 2022, 19:15
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በአገራዊ የምክክር ኮሚሽን የማዋቀር ሂደት ግልጽነትና ገለልተኝነት ላይ ቅሬታውን በመግለጽ ሂደቱ ለጊዜው እንዲቆም ጠየቀ።
የምክር ቤቱ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር ራሄል ባፌ የምክክር ኮሚሽኑን ለማቋቋም የተደረገው ሂደት ግልጽነት የጎደለው፣ ገለልተኛ እና አካታች ባለመሆኑ ምክር ቤቱ ቅሬታውን ለሚመለከታቸው አካላት ማቅረቡን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ ቅሬታውን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽህፈት ቤት እና ለምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ያስገባው ባለፈው የካቲት 03/2014 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባዔው ከተወያየ በኋላ ነው።
"ሂደቱ አስተማማኝ ካልሆነ የምንጠብቀውን ውጤት አያስገኝም" ያሉት ሰብሳቢዋ የጋራ ምክክሩ ለአገሪቷ ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ ኮሚሽነሮችን የመለየት እና የሹመት ሂደቱን ለጊዜው በማቆም እንደገና አካታችና ተዓማኒ ሂደት እንዲጀመር መጠየቃቸውን አስረድተዋል።
ከሁለት ሳምንት በፊት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለአገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከሕዝብ ከተጠቆሙ በመቶዎች ከሚቆጠሩ ግለሰቦች መካከል በዕጩነት የተለዩ የ42ቱን የስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በቀጣይ ሂደትም ከ42ቱ መካከል ለአገራዊ የምክክር ኮሚሽን በኮሚሽነርነት የሚሰየሙትን ለመለየት በቀረቡት ዕጩዎች ላይ ሕዝብ አስተያየት እንዲሰጥ ምክር ቤቱ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል።
የምክክር ኮሚሽኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ መሠረታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር በማድረግና ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ሂደትን የሚመራና የሚያስተባብር አካል ነው።
ከዚህ ቀደም የምክክር ኮሚሽኑ አዋጅ ላይ አስተያየት ለመስጠት የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ረቂቅ አዋጁን አቅርበው 53 የፖለቲካ ፓርቲዎች በተገኙበት መወያያታቸውን ያስታወሱት ዶ/ር ራሄል፤ በወቅቱ መሻሻል ያለባቸውን ነጥቦች ነቅሰው ማውጣታቸውንና ተጨማሪ ሃሳቦች መስጠታቸውን ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ እነዚህ የተነሱት ነጥቦች ሳይካተቱና ሳይስተካከሉ ወደ ዕጩዎች መለየት እና ሹመት ተገብቷል ብለዋል።
Continue reading https://www.bbc.com/amharic/news-60377980
የምክር ቤቱ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር ራሄል ባፌ የምክክር ኮሚሽኑን ለማቋቋም የተደረገው ሂደት ግልጽነት የጎደለው፣ ገለልተኛ እና አካታች ባለመሆኑ ምክር ቤቱ ቅሬታውን ለሚመለከታቸው አካላት ማቅረቡን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ ቅሬታውን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽህፈት ቤት እና ለምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ያስገባው ባለፈው የካቲት 03/2014 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባዔው ከተወያየ በኋላ ነው።
"ሂደቱ አስተማማኝ ካልሆነ የምንጠብቀውን ውጤት አያስገኝም" ያሉት ሰብሳቢዋ የጋራ ምክክሩ ለአገሪቷ ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ ኮሚሽነሮችን የመለየት እና የሹመት ሂደቱን ለጊዜው በማቆም እንደገና አካታችና ተዓማኒ ሂደት እንዲጀመር መጠየቃቸውን አስረድተዋል።
ከሁለት ሳምንት በፊት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለአገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከሕዝብ ከተጠቆሙ በመቶዎች ከሚቆጠሩ ግለሰቦች መካከል በዕጩነት የተለዩ የ42ቱን የስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በቀጣይ ሂደትም ከ42ቱ መካከል ለአገራዊ የምክክር ኮሚሽን በኮሚሽነርነት የሚሰየሙትን ለመለየት በቀረቡት ዕጩዎች ላይ ሕዝብ አስተያየት እንዲሰጥ ምክር ቤቱ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል።
የምክክር ኮሚሽኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ መሠረታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር በማድረግና ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ሂደትን የሚመራና የሚያስተባብር አካል ነው።
ከዚህ ቀደም የምክክር ኮሚሽኑ አዋጅ ላይ አስተያየት ለመስጠት የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ረቂቅ አዋጁን አቅርበው 53 የፖለቲካ ፓርቲዎች በተገኙበት መወያያታቸውን ያስታወሱት ዶ/ር ራሄል፤ በወቅቱ መሻሻል ያለባቸውን ነጥቦች ነቅሰው ማውጣታቸውንና ተጨማሪ ሃሳቦች መስጠታቸውን ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ እነዚህ የተነሱት ነጥቦች ሳይካተቱና ሳይስተካከሉ ወደ ዕጩዎች መለየት እና ሹመት ተገብቷል ብለዋል።
Continue reading https://www.bbc.com/amharic/news-60377980