ጠሚ ኢትዮጵያ ገዝፋባቸዋለች ወይም "too large to manage" ሆናባቸዋለች። ሰውዬው ብአዴንን የሚያክል "ነባር አገልጋይ" ለመጠቀም እንኳን አቅም እንዳነሳቸው ነው።
የመላው አማራ ህዝባዊ ሓይል
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ገዝፋባቸዋለች ወይም "too large to manage" ሆናባቸዋለች። የአቶ ፀጋ አራጌ ማመልከቻም ከብልፅግና ሞት ባሻገር የሚያሳየን ነገር ቢኖር ሰውዬው ብአዴንን የሚያክል "ነባር አገልጋይ" ለመጠቀም እንኳን አቅም እንዳነሳቸው ነው።
በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ስልጣናቸው ረጅም ግዜ እንደማይቆይ እሳቸውም የሚያጡት አይመስለኝም። ከዚህ በኋላ የእሳቸው ስልጣን ለአንድ ቀን መራዘም የሚያልቀውን አማራ ቁጥር ከመጨመር የዘለለ ፋይዳ ያለዉ የለዉም።
ቢያንስ ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው በመልቀቅ ለእውነተኛ ሽግግር መንገድ በመክፈት ሀገሪቷን እንዲታደጉ በትህትና እንጠይቃቸዋለን።
