Page 1 of 1
የማኅበረ ቅዱሳን የሃይማኖት ግጭት ጠመቃ በመ/ር ፋንታሁን ዋቄ አንደበት || ፖለቲካና ሃይማኖትን ስለምን ያደባልቃሉ?
Posted: 10 Feb 2022, 08:46
by sarcasm
የማኅበረ ቅዱሳን የሃይማኖት ግጭት ጠመቃ በመ/ር ፋንታሁን ዋቄ አንደበት || ፖለቲካና ሃይማኖትን ስለምን ያደባልቃሉ?
Re: የማኅበረ ቅዱሳን የሃይማኖት ግጭት ጠመቃ በመ/ር ፋንታሁን ዋቄ አንደበት || ፖለቲካና ሃይማኖትን ስለምን ያደባልቃሉ?
Posted: 11 Feb 2022, 01:02
by Naga Tuma
ተዋህዶ ስለ ማህፀን ቃል ያለዉ ቃሉ ኣፈራች? ቃሉ የማይቀለበስ ቃሉን ኣከብራለሁ።
መንግስት ከሃይማኖት ገለልተኝነትን ፅንሰሀሳብንም ኣከብራለሁ። ኣንዱ ከሌላኛዉ ገለልተኛ ይሁን ማለት ሁለቱ መደጋገፍ ኣይችሉም ማለት ኣይዴለም። የኣሜሪካዉ የስለላ ድርጅት እና የካቶሊክ ሃይማኖት ዋና መቀመጫ ቫቲካን የሚደጋገፉ መሆናቸዉን ከስድስት ኣመታት በፊት ማንበቤን ኣስታዉሳለሁ። ኣንዱ ከሌላዉ ገለልተኛ ሆነዉ ይታወቃሉ።
እንደሚገባኝ ከሆነ በኣዉሮፓ የገለልተኝነትን ፅንሰሀሳብ ኣምጦ የወለደዉ የካቶሊክ ሃይማኖት ኢምክንያታዊ እልቂት መብዛት ነዉ።
ምክንያታዊ መሆን መጀመር የኣዉሮፓ ትራንስፎርሜሽን የሚባለዉን ወለደ። የእግዝኣብሔር መንግስት በሰዉ ዉስጥ መሆኗን ማስተዋል የዚህ ትራንስፎርሜሽን መሰረት ነዉ ተብሎ የታወቃል።
ምክንያታዊ ከሆኑት ደግሞ የህዳሴ ወይም ሬይነሳንስ ሰዎች ተፈጠሩ። እንደዛ ኣይነት ሰዎች ያስተዋሉትን ማስተዋል እንጂ በቀላሉ መቀልበስ የሚቻል ኣይመስለኝም። ኣስፈላጊም ኣይመስለኝም። ስለዚህ ርዕስ ኣንድ ጊዜ ከሆረስ ጋር እዚህ መድረክ ላይ መከራከሬን እና መናገሬን ኣስታዉሳለሁ።
የኣዉሮፓ ትራንስፎርሜሽን ኣህጉሩን ከኢምክንያታዊ የጭለማ ዘመን ወደ ምክንያታዊ ኣብርሆት ኣሸጋገራቸዉ። ከዛም ኣደጉ።
የሃገራችን የቦረና ማህበረስብ ተመሳሳይ ስልጣኔን ከጥንት ጀምሮ ኣስተዉሏል ስንል ያለምክንያት ኣይዴለም። የማህበረሰኑን ዕዉቀት የነበረዉ የቦረና ኣዛዉንት ስለገዳ ስርዓት ከቃሉ መዋቅር ገለልተኝነት ኣስተምሯል። የገዳ ስርዓት መሪዉን ይሾማል። ቃሉ የመሾሙ ሂደት ዉስጥ ጣልቃ ሳይገባ የተሾመዉን ይቀባል፣ ይባርካል እንደማለት ይሆን? የሳትኩኝ ካለ ለመታረም ዝግጁ ነኝ።
ስለዚህ የገለልተኝነት እና መደጋጋፍ ፅንሰሀሳብ እኛም ጋ የነበረ፣ ኣዉሮፓ ከብዙ ዘግናኝ ዕልቂቶች በሁዋላ የተስተዋለ፣ ኣሜርካ የተተከለ ነዉ ቢባል ስህተት ኣይመስለኝም።
መምህሩ መደጋገፍ ላይ ያተኮሩ ይመስላል። ሲሿሿሙ በገለልተኝነት ሆኖ የተሾሙት መተዋወቅ ኣይችሉም የሚሉ ኣይመስለኝም።
Re: የማኅበረ ቅዱሳን የሃይማኖት ግጭት ጠመቃ በመ/ር ፋንታሁን ዋቄ አንደበት || ፖለቲካና ሃይማኖትን ስለምን ያደባልቃሉ?
Posted: 09 Mar 2022, 09:15
by sarcasm
Please wait, video is loading...