Page 1 of 1

''ድንገት በመሃል ጨዋታ ላይ ፌስቡኩን ከፍቶ እየጎረጎረ - 'ስብሃት ነጋ ተፈታ እኮ!' አይለኝም? ይኸው ተናድጄ፣ ተቃጥዬ፣ አብጄ፣ ጨጓራዬ ተነስቶብኝ በአምቡላንስ ነው ሆስፒታል የሄድኩት።

Posted: 06 Feb 2022, 20:32
by sarcasm
By Eyob Mihreteab Yohannes
·
(100% እውነተኛ ታሪክ ነው)
∞ ∞ ∞ ∞ ∞ ∞
አንድ ውጪ የምትኖር የማውቃት ሴትዮ በስንት ጊዜዋ በWhatsApp ደውላልኝ የባጥ የቆጡን ስናወራ ስናወራ፣ አፌ ላይ እንዴት እንደመጣልኝ አላውቀውም፤ 'የገናን በአል ዶሮ ሰርተሽ አከበርሽው ወይ?' አልኳት።
(እሷ) - ''ኧረ ተወኝ። ገናንማ ታምሜ፣ ሆስፒታል ገብቼ ነው ያሳለፍኩት''
(እኔ) - ''ምን ሆንሽብኝ?''
(እሷ) - ''እኔማ በአል ነው ብዬ፣ ዶሮ ክትፎ ሰርቼ ዘመድ ተሰብስቦ እየበላ እየጠጣ ሳለ ያ ጉደኛው ባሌ መርዶዬን አረዳኛ!''
(እኔ) - ''ማለት?''
(እሷ) - ''ድንገት በመሃል ጨዋታ ላይ ፌስቡኩን ከፍቶ እየጎረጎረ - 'ስብሃት ነጋ ተፈታ እኮ!' አይለኝም? ይኸው ተናድጄ፣ ተቃጥዬ፣ አብጄ፣ ጨጓራዬ ተነስቶብኝ በአምቡላንስ ነው ሆስፒታል የሄድኩት። . . . በበአል ቀን አዋረደኝ የገዛ ባሌ።''
(እኔ፣ ከምር አዝኜ) - ''ውይ ሲደብር። ምን ስብሃት ዘመድ ምናምን ገድሎብሽ ነበር ወይ?''
(እሷ) - ''እንዴ?! ዋናው የጥፋት ስትራቴጂስት እሱ ነው አልተባለም እንዴ? የህወሃት ስትራቴጂስት ነው ሲባል አልነበር ወይ? . . . ዘመዶቼንማ የታባቱ አግኝቶ ይገድልብኛል!''
(ተናድጄ) - ''አንቺ ግን በሽተኛ ነሽ ጤነኛ?!''
(እሷ) - ''ለነገሩ አንተም ትግሬ አይደለህ? ያው ናችሁ። ያው ናችሁ እኮ!'' 😁😁😁😁
¤
. . . በነገራችን ላይ ልክ ነች፣ ትግሬ ነኝ። (ነኛ!)
ያው ሐማሴን ከሠራዬ፣ ከአከለጉዛይ፣ ከአጋመና ከአድዋ ከፍ ያለ ምርጥ ዘር ስለሆነ ብዙም አናወራውም። እንጂ የጠራ የኮራ ትግሬ ሐማሴን ነው። ኤቲስትነቴን ይንሳኝን ከምሬን ነው! 😁😁
¤
Please wait, video is loading...

Re: ''ድንገት በመሃል ጨዋታ ላይ ፌስቡኩን ከፍቶ እየጎረጎረ - 'ስብሃት ነጋ ተፈታ እኮ!' አይለኝም? ይኸው ተናድጄ፣ ተቃጥዬ፣ አብጄ፣ ጨጓራዬ ተነስቶብኝ በአምቡላንስ ነው ሆስፒታል የሄድ

Posted: 06 Feb 2022, 20:42
by sebdoyeley
sebdoyeley wrote:
06 Feb 2022, 18:05
sebdoyeley wrote:
30 Jan 2022, 03:54