ከባድ ጊዜ እየመጣ ነው..! ከዚህ በኋላ መንግስት እያተመ በሚረጨው ብር ደግሞ ገና ብሩ ይረከሳል፤ ኑሮውም ጣራ ይነካል፡
Posted: 03 Feb 2022, 08:40
ከባድ ጊዜ እየመጣ ነው..!
By Tsegaw Melaku
·
የገንዘብ ሚኒስቴር በሰሜን ኢትዮጵያ ከአውዳሚው ጦርነት ጋር በተያያዘ ተጨማሪ ወጪ በማስፈለጉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካኝነት የ122 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት አፀድቋል፡፡ የበጀቱ ምንጭ ከየት ነው ሲባል፡፡ ከሀገር ውስጥ ብድር ብድር መሆኑን የጸደቀው የበጀት አዋጅ ያመለክታል፡፡
ከሀገር ውስጥ ምንጮች መንግስት ተበደረ ማለት ፤ ባጭሩ ገንዘብ ማተም ውስጥ ገባ ማለት ነው፡፡ ይህ ከሆነ ገንዘቡ እየረከሰ ኑሮው እየተወደደ መሄዱ አይቀሬ ነው፡፡ መንግስት ታክስ መሰብሰቡ ላይ ከመሟትና መንግስታዊ ቁጠባ ውስጥ ከመግባት ይልቅ ብድሩን መርጧል፡፡ ይህም እያንዳንዱ ዜጋ በዋጋ ንረት ወይንም ግሽበት ኢኮኖሚ ጫና ውስጥ እንዲገባ የሚያድርገው ነው የሚሆነው፡፡ ይህ የግሽበት አዙሪትም ባለፉት ሁለት ወራት ጀምሯል፡፡
.
በኢትዮጵያ የታኅሣሥ ወር የዋጋ ንረት ከ35 በመቶ እንዳለፈ እና በኅዳር ወር ከነበረበት በ21 በመቶ እንደጨመረ የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታትስቲክስ አገልግሎት ከሁለት ሳምንት በላይ ዘግይቶ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
የምግብ ዋጋ ንረቱ በኅዳር ወር ከነበረበት 38 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 41ነጥብ 6 በመቶ ያሻቀበ ሲሆን፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ሸቀጦች የዋጋ ንረት ደግሞ ከ25 ነጥብ 2 በመቶ ወደ 26 ነጥብ 6 በመቶ አሻቅቧል። በታኅሣሥ ወር የተመዘገበው የዋጋ ንረት በአገሪቱ በ10 ዓመታት ውስጥ ከፍተኛው መሆኑ ታውቋል::
ከዚህ በኋላ መንግስት እያተመ በሚረጨው ብር ደግሞ ገና ብሩ ይረከሳል፤ ኑሮውም ጣራ ይነካል፡፡ ከዚህ ሁሉ ጣጣ መንግስታዊ ብክነቱ ቢቀንስ፣ መንግስት የታክስ መሰረቱን አስፍቶ ቢሰበስብ የተሻለ ይሆን ነበር፡፡ ግን ደግሞ ሩጫው ሌላ ሆኗል፡፡
By Tsegaw Melaku
·
የገንዘብ ሚኒስቴር በሰሜን ኢትዮጵያ ከአውዳሚው ጦርነት ጋር በተያያዘ ተጨማሪ ወጪ በማስፈለጉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካኝነት የ122 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት አፀድቋል፡፡ የበጀቱ ምንጭ ከየት ነው ሲባል፡፡ ከሀገር ውስጥ ብድር ብድር መሆኑን የጸደቀው የበጀት አዋጅ ያመለክታል፡፡
ከሀገር ውስጥ ምንጮች መንግስት ተበደረ ማለት ፤ ባጭሩ ገንዘብ ማተም ውስጥ ገባ ማለት ነው፡፡ ይህ ከሆነ ገንዘቡ እየረከሰ ኑሮው እየተወደደ መሄዱ አይቀሬ ነው፡፡ መንግስት ታክስ መሰብሰቡ ላይ ከመሟትና መንግስታዊ ቁጠባ ውስጥ ከመግባት ይልቅ ብድሩን መርጧል፡፡ ይህም እያንዳንዱ ዜጋ በዋጋ ንረት ወይንም ግሽበት ኢኮኖሚ ጫና ውስጥ እንዲገባ የሚያድርገው ነው የሚሆነው፡፡ ይህ የግሽበት አዙሪትም ባለፉት ሁለት ወራት ጀምሯል፡፡
.
በኢትዮጵያ የታኅሣሥ ወር የዋጋ ንረት ከ35 በመቶ እንዳለፈ እና በኅዳር ወር ከነበረበት በ21 በመቶ እንደጨመረ የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታትስቲክስ አገልግሎት ከሁለት ሳምንት በላይ ዘግይቶ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
የምግብ ዋጋ ንረቱ በኅዳር ወር ከነበረበት 38 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 41ነጥብ 6 በመቶ ያሻቀበ ሲሆን፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ሸቀጦች የዋጋ ንረት ደግሞ ከ25 ነጥብ 2 በመቶ ወደ 26 ነጥብ 6 በመቶ አሻቅቧል። በታኅሣሥ ወር የተመዘገበው የዋጋ ንረት በአገሪቱ በ10 ዓመታት ውስጥ ከፍተኛው መሆኑ ታውቋል::
ከዚህ በኋላ መንግስት እያተመ በሚረጨው ብር ደግሞ ገና ብሩ ይረከሳል፤ ኑሮውም ጣራ ይነካል፡፡ ከዚህ ሁሉ ጣጣ መንግስታዊ ብክነቱ ቢቀንስ፣ መንግስት የታክስ መሰረቱን አስፍቶ ቢሰበስብ የተሻለ ይሆን ነበር፡፡ ግን ደግሞ ሩጫው ሌላ ሆኗል፡፡
Please wait, video is loading...
https://www.facebook.com/tsegaw.melaku. ... 8429580863


