ስንት ማፈሪያ አለ? ኢትዮጵያ ከአጎዋ በመሰረዝዋ ወደ 78% የሚሆን የቆዳ ውጤት ወደ ውጭ መላክ አልቻለችም
Posted: 16 Jan 2022, 13:42
እነዚህ ሰዎች የሚያስብ ጭንቅላት አላቸው ወይ? ሁለመናቸው ከ ሀ እስከ ፐ የተሰራው በእርዳታ ነው:: በሰው ትከሻ ካልኖሩ ያማቸዋል::
78% የቆዳ ምርት የተባለው ጫማ እና ሌሎች የቆዳ ውጤቶች ናቸው :: ይህን እኮ አገር ውስጥ ገበያውን እንዲቆጣጠር ማረግ ይቻላል:: በተለይ 100 ሚልዮን ሕዝብ የአገሪቱን ጫማ እንዲገዛ ማስገደድ ነው :: ሌላ ምን ይፈልጋሉ? የውጭውን ገበያ ማስወጣት ነው:: ደሞም እኔ እስካሁን የምገዛው የአገር ምርት ነው: ጥራትም አለው::
ከአጎዋ የቀረባቸው 200 ሚልዮን ዶላር አይደል? ይህ በሌላ መንገድ መተካት አይቻልም?
ለዚህ ነው ተዋርደው የሚያዋርዱን?
አያቶቻችን እንዲህ የተዋረዱ እና እኛን የሚያዋርዱ አልነበሩም ::