ኣሁን ከድሉ ጎን ለጎን ትምህርት መሰረት ያደረገ የኢትዮጵያ ዳግመ-ትንሳኤ መመስረት ኣለበት። በነጮች የምትናቀውና የምትገደለው ዘመናዊ እውቀት የራስህን ስላላደረግህ ነው።
Posted: 22 Dec 2021, 13:30
ጓላ-ቀርነት የራሱ መዘዝ ይጠራል
ኣሁን ከድሉ ጎን ለጎን ትምህርት መሰረት ያደረገ የኢትዮጵያ ዳግመ-ትንሳኤ መመስረት ኣለበት። በነጮች የምትናቀውና የምትገደለው ዘመናዊ እውቀት የራስህን ስላላደረግህ ነው። ግብጻውያን የሃይማኖት ኣባቶችና ሊሂቃን ከየፈረንሳ ዘመቻ ( ኣል-ሓምላ ኣል-ፊረንሲያ ) በጓላ ተመሳሳይ ጥያቄ ኣንስተው ነበር ምክንያቱ ጥቂት መሳርያ የያዙና በተለያየ የእውቀት መስኮች ፈሊጣዎች የሆኑ - የሃገሪቱን ታሪካዊና ተፈጥሮኣዊ ይዞታ ለመመርመር - ኣገሩን በቀላል ወረው ስለ ገቡ ።
በየመንደሩ ስንት እንክብካቤ ያላገኘ ጭንቅላት ያለው ህጻን ይኖር ይሆናል ? በትምህርት ብቻ ሳይሆንም ለምሳሌ በእግር-ኳስም ሊሆን ይችላል ። ልዩ ችሎታ ( ታለንት ) በየክለብ ደረጃ በሚጫወቱ ንቁ ( ኣክቲቭ ) የሆኑ ሰዎቻ ብቻ ሊታጠር ኣይችልም ። በኣጭሩ ከንግዲህ በጓላ የኣስተሳሰብ መቀየር ሊያስፈልግ ነው ። ኣንዳንዶች እንግሊዘኛና ኣማርኛ የሚደባልቁ እንደ ሚሉት ፥ It is a must !!
.