።
ከልብ የሆነ ይቅርታ እጠይቃለሁኝ
በአምባሳደር ብርሃነ የተመራውና ወዳጆቼ ዶክተር እሌኒና ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅና ሌሎች የቅርብ ወዳጆቼ በተሰበሰቡበት የሽግግር መንግስቱ ሚስጥራዊ ስብሰባ ላይ የስብሰባው አባል ብሆንም ባለመገኘቴ ይቅርታ እጠይቃለሁ ። ልገኝ ያልቻልኩበት ምክንያት ሌላ የሽግግር መንግስት በነያሬድ ጥበቡና በነታምራት ላይኔ ስለተቋቋሙና እሱ ውስጥ አባል ስለሆንኩኝ ነው ።
ቅዳሜ ደግሞ በነፕሮፌሰር ሕዝቅያስ የተመሰረተ ሌላ የሽግግር መንግስት ውስጥ በአባልነት ተሳትፌያለሁ ። እነሀብታሙ አያሌውም የእኛ የሽግግር መንግስት አባል ሁን እያሉኝ ነው ። እስካሁን ድረስ አስራ አምስት የተለያዩ ሽግግር መንግስቶች ውስጥ አባል ስለሆንኩ ጊዜ ሊበቃኝ አልቻለም ። እንደመፍተሄ የሽግግር መንግስቶቹን የሚያሸጋግር የሽግግሮች ሽግግር አሰባሳቢ በቅርቡ ሁላችሁንም እጠራችኋለሁ ።
Please wait, video is loading...