Ethiopian Broadcasting Corporation
Nov 21 2021
ከደባርቅ ወደ ጎንደር ተጭኖ ሊወጣ የነበረ ከ7,000 በላይ የሆነ ተተኳሽ የብሬንና የክላሽ ጥይት፣ አንድ ክላሽን ኮቭ ጠብመንጃ፣ በቁጥጥር ስር ዋለ
*********************
የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጋር ባደረገው የተጠናከረ ክትትል ብዛቱ ከ7 ሽህ በላይ የሆነ ተተኳሽ የብሬንና የክላሽ ጥይት፣ አንድ ክላሽን ኮቭ ጠብመንጃ፣ ልዩ ልዩ የባንክ የሂሳብ ደብተሮች፣ ሲም ካርዶች እና የብሬን አንገት በደባርቅ ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
በጎንደር ከተማ የቀበሌ 15 ነዋሪ የሆነው ፍጹም ገብረ ክርስቶስ በሰሌዳ ቁጥር 03 አማ - 25162 በሆነ ሚትስቡሽ ፒክ አፕ መኪና ለጸጥታ አካላት የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠሁ ነው በማለት በተከዜ ግንባር ከሳምንት በላይ ሲንቀሳቀስ መቆየቱ ተገልጿል፡፡
ግለሰቡ ወደ ዛሪማ በሚመላለስበት ወቅት የወገንን ሃይል አሰላለፍና የከባድ መሳሪያዎችን አቀማመጥ ለጠላት መረጃ አሳልፎ ሲሰጥ እንደቆየና አሁንም በመኪናዋ ላይ ሞደፊክ ባሰራው የሕገ ወጥ እቃዎች መጫኛ ተተኳሾችን ከዛሪማና ከደባርቅ በመሰብሰብ ወደ ጎንደር ወስዶ ለቅማንት ጽንፈኛ ቡድን ለማቀበል ስምምነት እንደነበረው መናገሩን ከሰሜን ጎንደር ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
Please wait, video is loading...