Page 1 of 1

"የኣብይ ኣህመድ መንግስትና ደመቀ መኮንን የሚመራው ተስፋፊ ልሂቅ ጦርነቱ በነሱ ተሸናፊነት እንደሚጠናቀቅ በትክክል ኣውቀውታል" ጌታቸው ረዳ

Posted: 18 Nov 2021, 09:23
by sarcasm
የኣብይ ኣህመድ መንግስትና ደመቀ መኮንን የሚመራው ተስፋፊ ልሂቅ በትግራይ ህዝብ ላይ የጀመሩት የዘር ማጥፋት ጦርነት በወታደራዊ መስኩ በነሱ ተሸናፊነት እንደሚጠናቀቅ ኣብይም ደመቀም በትክክል ኣውቀውታል:: ይሁን እንጅ ኣዲስ ኣበባ ውስጥም 'ቀኝ ግራ' የሚል ስልጠና ሰጥተውና ኣስፋልት ዳር ምሽግ ሰርተው ተጨማሪ ደም መፋሰስ ለመፍጠር የሚቻላቸውን እያደረጉ ይገኛሉ:: በፍፁም ኣይሆንላቸውም ከነፉከራቸው መቀመቅ ይወርዷታል:: የኛ ሰራዊት መንዝና ግሼ ከገባ በሁዋላ ጭምር የወሎ ግንባር እያሉ ደጋፊዎቻቸውን የሚያጨብረብሩት የኣብይ ተላላኪዎች ሽንፈታቸውን ላለመቀበል የሚያነሷቸው ሦስት ኣስቂኝ ምክንያቶች ኣሉ::

ኣንደኛ: ሰራዊቱ በኣሻጥር ምክንያት ያለውግያ በመፈርጠጡ ቦታ ለቀቅን እንጅ በውግያ ኣልተሸነፍንም ይላሉ:: እስካሁን ያለቀው በኣስር ሽዎች የሚቆጠር ወታደር: ልዩ ሃይል: ሚሊሻና ፋኖ ተራ ኣሃዝ ነው:: ታንኩና መድፉን እርሱት:: ለነገሩ ኣሻጥርን ያስቻለን እውነታ የፈጠረ ፖለቲካ ካለ ደግሞ የራሳቸው ራስ ምታት ነው::

ሁለተኛ: ወያኔ/ጁንታው መዘዞየደረሰው በውግያ ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ ነው የሚል ተረት ነው:: ይህንን ለመቋቋም ደግሞ በቁጥጥራችን ስር የገቡ ከባቢዎችን ህዝብ ወሬ የፈታው ባንዳ እያሉ ማብጠልጠል ይዘዋል:: ሰራዊታችን የደረሰበት ቦታ ላይ የደረሰውና ኣሁንም በፍጥነት በመገስገስ ላይ የሚገኘው ከፀረ ህዝብ ሰራዊት ጋር ገጥሞ በሚገባ ኣሸንፎ ነው:: ግብኣተ መሬታቸውን የምናረጋግጠውም የቀረውን ሃይላቸውን ደምስሰን ነው:: እስካሁን በተደረገው ውግያ የተሸነፈው የኣማራን ህዝብ ጭምር ለሞትና እንግልት የዳረገውን ፀረህዝብ ሰራዊት እንጂ ያማራ ህዝብ ኣይደለም::

ሦስተኛ: ኣሁን እየተደረገያለው ጦርነት በምዕራባውያን ጣልቃገብነት የሚደገፍና ኣፍሪካውያንን ኣንገት ለማስደፋት የታሰበ ዘመቻ ነው የሚል ነው:: በነገራችን ላይ ኣብይ ኣህመድ የምዕራባውያን ዋና ተላላኪ ሆኖ ኖቤል መሸለሙን ረስቷል:: ኣብይ ኣህመድ ኢሳያስ ጋር 'የሰላም ስምምነት' ጀዳ ውስጥ ሲፈራረም የወቅቱ የኣፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የነበሩት ፖል ካጋሜ በስነስርዓቱ ላይ እንዲገኙ የሳውዲ ኣረብያ መንግስት ያደረገላቸውን ጥሪ እንዲሰረዝ ያደረገ መሆኑን ኣብዛኛው ኣፍሪካ ኣይዘነጋም:: ኣሁን ደርሶ ኣፍሪካ ወይም ሞት ከውድቀት ኣያድንም:: ለማንኛም ልጆች ሆነን ያልታሰበ ሽንፈት የገጠመው የሰፈር ጉልቤ የቀጠቀጠውን ኮስማና ልጅ ድል ላለመቀበል ሌላ ሃገር ያለን ጉልቤ ተጠያቂ እንደሚያደርገው ዓይነት ነው:: ለማንኛውም ኣብይ ለውድቀቱ Uncle Samን ተጠያቂ ስላረገ የትግራይና የኦሮሞን ሰራዊት ድል ኣያሳንስም::

በነገራችን ላይ ከእውነት ጋር ሳይታረቁ መቃብር ለሚወርዱት ሽፍቶች ፃድቃኔ ማርያም ትሁናቸው ከማለት ውጭ ምንም ማለት ኣይቻልም::

ትግራይ ትስዕር!
Please wait, video is loading...

Re: "የኣብይ ኣህመድ መንግስትና ደመቀ መኮንን የሚመራው ተስፋፊ ልሂቅ ጦርነቱ በነሱ ተሸናፊነት እንደሚጠናቀቅ በትክክል ኣውቀውታል" ጌታቸው ረዳ

Posted: 18 Nov 2021, 09:56
by Sam Ebalalehu
It is essential to remind Getachew what was going on. He seemed to have failed to understand it. The fight that has been going on is between Ethiopia on one side and TPLF and OLF “ Shene” on the other. Abiy and Demke are simply just two people who choose to be on the side of Ethiopia.