t0uo5t9g05a6m10g065m75 ·
አክቲቪስት ታማኝ በየነ ወገኔ በሚጨነቅበት ወቅት አብሬው ከሌለሁ ኢትዮጵያዊነቴ ትርጉም የለውም አለ።
#Ethiopia : ወገኔ በሚጨነቅበት ወቅት አብሬው ከሌለሁ የእኔ ኢትዮጵያዊነት ትርጉም የለውም ሲል የሰብኣዊ መብት ተሟጋችና አክቲቪስት ታማኝ በየነ ተናገረ።
አክቲቪስቱ ወደ አገሩ መመለሱን በማስመልከት ለጋዜጠኞች መግለጫ እየሰጠ ነው።
በመግለጫው አገሬን በክፉ ቀኗ አብሬያት ካልሆንኩ ደግሜ አገሬን ለመመልከት የሚያስችል ሞራል ሊኖረኝ አይችልም ብሏል።
አሸባሪውን ሕወሓትን ሴራ ያልተናገርኩበት ወቅት የለም ያለው ታማኝ አሁን ግን ርህራሄ የማያውቅ ክፉ መሆኑን ማረጋገጫ ሰጥቷል ሲል ተናግሯል።
አክቲቪስት ታማኝ ሁሉም ሕዝብ አብሮ በመሆን አሸባሪውን ቡድን ማጥፋት እንደሚገባውም ጥሪ አቅርቧል።
