የ ገበሬውን በሬ አርዶ ሊበላ ያሰፈሰፈው ረሃብተኛ ወራሪ ሽፍታ፥ በአየር ሃይል አመድ ሆነ፥
Posted: 22 Oct 2021, 14:54
የውሎ ሪፖርት
አሳዬ ደርቤ
⓵ ወረባቦ ጎሃ ትምህርት ቤት አካባቢ የአርሶ አደሩን በሬ አርዶ ጥብስ ለመብላት ሲዘገጃጅ የነበረው አሸባሪ አየር ሃይላችን በወረወረው መብረቅ ገላው ተጠባብሶ እንዳይሆኑ ሆኗል!
⓶ ወሎን ሊዘርፍ በ22 ተሳቢ ተጭኖ የመጣው አሸባሪም መኪናው ላይ ታጭቆ የሚዘርፈውን የሐይቅ ከተማ አሻግሮ እያዬ ሳለ አየር ሃይላችን ከሰማይ በደፋበት እሳት ከመኪናው ሳይወርድ ተረፍርፏል፡፡
⓷ ወደ ደሴ ለመግባት አስቦ በቦሩ በኩል ወረራ የፈጸመው ጉጅሌ በጀግኖቹ ክንድ ተደቁሶ ደሴን ለመቆጣጠር እንደናፈቀ ወደ መቃብር ተሸኝቷል፡፡
⓸በአፋርና በአማራ በኩል ወረራ ፈጽሞ እልፍ አእላፍ ጓዶቹን የተጠነቀው ትርፍራፊ ጦር የአዛዦቹን ትዕዛዝ ተቀብሎ ወደ መቃብር በመውረድ ፈንታ ‹‹ሞት በቃኝ›› ብሎ አፈሙዙን ወደ አለቆቹ ማዞር ጀምሯል፡፡
⓹መቀሌ ላይ ተቀምጠው የሰማይ አሞራ ሳይቀር የሚያስበረግጋቸውና ህልማቸው መክሸፉን የተረዱት የአሸባሪው ቡድን መሪዎችም አሁን ከመሼ ‹‹አሸንፈናል›› በሚል ፉከራ ጀምሮ ‹‹ታደጉን›› በሚል ልመና የሚጠናቀቅ መግለጫ ለማውጣት ተገድደዋል፡፡
‹‹ማርከን እና ገድለን›› በሚል የድል ዜና የሚጀምር መግለጫቸውን ‹‹የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ ሽንፈት የተጎነጨ መንግሥትህን በቃህ ብለህ አስጥለን›› በሚል ልመና የሚደመድም መግለጫቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
በወገን በኩል ደግሞ…
ስለሆነም ደቡብ ወሎ ላይ የተሰነዘረው ጥቃት ተቀልብሶ ሰሜን ወሎን ነጻ የምናወጣበት መሆኑ እርግጥ ነውና የደሴና የኮምቦልቻ ወጣቶች ለሠራዊታችን ደጀን የመሆን ተግባራችሁን አጠናክራችሁ ቀጥሉ!
ድል ለእኛ!
Share