Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Abaymado
Member
Posts: 4617
Joined: 27 Sep 2017, 21:56

የኢትዮጵያ ግብርና ሚንስቴር የከሸፈ መስሪያ ቤት ነው!! እንደገና ቢዋቀርስ? አገሪቱን cassavaን የመሳሰሉ የምግብ እህሎችን ከውጭ እንዳታመጭና እንዳተበቅይ ያላት ማነው ?

Post by Abaymado » 12 Sep 2021, 07:30


አሁን አገሪቱ ውስጥ ግብርና ሚንስቴር አለ የሚባልበት አገር ላይ አይደለንም:: ቢያንስ ቢያንስ በምግብ ራሳችንን ቻልን ተብሎ በሚሰበክበት ሰዓት ያሉን የምግብ እህሎች እስከነጭራሹ ብልሽትሽታቸው እየወጣ ነው::

ጥሩ ሙዝ በአሁኑ ሰዓት እዚህ አገር ላይ ማግኘት ዘበት እየሆነ ነው:: በጣም ቀጫጫ: ሲያዩት የሚያስጠላ ሙዝ ነው ያለው:: መንግስት የዚህን ችግር ለማጥናት ሞክሯል?
ቡርትካንማ አይታሰብም:: በፊት በሁለት ብር ሁለት ኪሎ ምን የመሰለ ቡርትካን ይገዛ ነበር:: አሁን 60 ብር ተከፍሎ የሚገኘው ለዛውም ከተገኘ አንድ ኪሎ ሎሚ ሎሚ የሚል ቡርትካን ነው:: መንግስት የዚህን የቡርትካን መጥፋት ምክንያትስ ያጠና ይሆን?

ሌላው ደሞ የሚገርመው ነገር ጤፍ ከኢትዮጵያ ውጥቶ ሌላው አገር እየበቀለ ሲሆን: ኢትዮጵያ ግን ሌላው አገር ብቻ የሚበቅለውን አምጥታ ማብቀል እንደ ውርደት የምትቆጥር አገር ትመስላላለች:: ምንድነው ችግሩ?

ለምሳሌ cassava እኛ አገር መኖሩን እጠራጠራለሁ: ለምን የለም? ይህ አገራችንን የሰውን አገር እርዳታ ከምትጠባበቅ ይገላግላት ነበር:: ካሳቫ ለሁሉ ነገር የሚሆን ምግብ ነው::