ለሕልውና ትግሉ ሴት ወንዱ ተሰልፏል። መሳርያ ሳይዙ በዱላ፣ በድንጋይ፣ በመጥረቢያ ከጠላት ጋር ተናንቀው መሳርያ የሚማርኩ ጀግኖች ሞልተዋል። ይህን ጀብዱ የሚፈፅሙት ግን ወንዶች ብቻ አይደሉም። ሴቶችም ገራሚ ጀብዱ እየሰሩ ነው። የሰሜኗ ጀግኒት ምሳሌ ነች!
በፎቶው የምትታየው አስቴር ትባላለች። የደባርቅ ከተማ ነዋሪ ነች። አሸባሪው ትህነግ "ደባርቅን ተቆጣጠርኩ" ወዘተ ብሎ በሀሰት ሲያስወራ ቀየዋን ጥላ አልሸሸችም። ጭራሽ ከሰራዊቱ ጋር ሆነ ጠላት ወዳለበት ቦታ ሄደች። መሳርያ ሳትይዝ ጀሌ ሆና፣ የወገን ጦርን ልታግዝ፣ በድንጋይም ቢሆን ጠላትን መትታ መሳርያ ልትታጠቅ ወደ ጦር ግንባር አቅንታለች። የጦር ግንባር ከባድ መሳርያ ሲጮህበት የሚውል ነው። የጥይት ሩምታ የሚወርድበት ነው። ቁስለኛና ሙት የሚበዛባት ነው። ሳትፈራ ያውም ባዶ እጇን፣ አንዱን መሳርያ እቀማዋለሁ ብላ ነው የዘመተችው።
የወገን ጦር ጋር በነበረችበት ወቅት በቅርብ ያለ የወገን ዲሽቃ ተኳሽ ይቆስላል። የአሸባሪው ትህነግ ታጣቂ ዲሽቃ ተኳሹ መቁሰሉን አይቶ መሳርያውን ሊያነሳ ሲመጣ ባዶ እጇን የሄደችው አስቴር በድንጋይ መትታው ጠላትንም የወገንን መሳርያ አስቀርታለች። መከላከያ ሰራዊቱም ለዚህ ጀብዷ መሳርያ አስታጥቋታል።
ቤቱ ቁጭ ያለ፣ መከላከያን ተቀላቀል ተብሎ የሚለመን ወንድ፣ ያውም አፍለኛ ወጣት ሞልቷል። ሴቷ አስቴር ግን ሳታወላውል ከሰራዊቱ ጋር የሕልውና ዘመቻን ተቀላቀለች። ቤት ቁጭ ብላ በሀሰት ወሬ መጨነቅ አልፈለገችም። እስከ አፍንጫው ታጥቆ የሚሸሽ ወንድ ይኖራል። አስቴር ግን በባዶ እጇ ጠላትንና የወገንን መሳርያ ታስቀራለች። ቀየዋን ጥላ ከመሸሸት ወደ ፊት ሄዳ ጠላት ያለበት ድረስ ውሎዋን አድርጋ ጀብድ ፈፅማለች

