ethiopiainsider
በሃሚድ አወል

የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ፍርድ ቤት፤ በአፋር ክልል አዋሽ ሰባት ኪሎ ከተማ በእስር ላይ በሚገኙ ሶስት ጋዜጠኞች ላይ ለአራተኛ ጊዜ የምርመራ ጊዜ ፈቀደ። ፍርድ ቤቱ የምርመራ ጊዜውን የፈቀደው የአውሎ ሚዲያ ዋና አዘጋጅ በሆነው በቃሉ አላምረው፣ በሚዲያው ላይ በተንታኝነት በሚሳተፈው ፋኑኤል ክንፉ እንዲሁም የ“ኢትዮ ፎረም” ጋዜጠኛ በሆነው አበበ ባዩ ላይ ነው።
የወረዳው ፍርድ ቤት ለዛሬ ነሐሴ 6፤ 2013 ቀጥሮ የነበረው፤ ፖሊስ ባለፈው ችሎት በተፈቀደለት አስር የምርመራ ቀናት ያከናወናቸውን ተግባራት ለመስማት ነበር። ነገር ግን ፖሊስ “ምርመራዬን አላጠናቀቅኩም” በማለቱ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አራት የምርመራ ቀናት መፍቀዱን የጋዜጠኞቹ ጠበቃ አቶ ታደለ ገብረመድሀን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
Continue reading https://ethiopiainsider.com/2021/4197/