Page 1 of 1

ኢትዮጵያ የ10000 ሜትር ወርቅ አጣች! የኢትዮጵያ ዝርያዎች ግን አለምን አስደነቁ !!

Posted: 07 Aug 2021, 09:39
by Horus
አንዷ ኢትዮጵያዊት ሲፋን ሃሰን ለኔዘርላንድ ሮጣ ፈረንጅ ወርቅ አገኘ!
ሌላዋ ኢትዮጵያዊት ቃል ኪዳን ገዛሃኝ ለባህሬን ሮጣ አረብ ብር አገኘ!
ሌላዋ ለተሰንበት ግደይ ለኢትዮጵያ ሮጣ ኢትዮጵያ መዳብ አገኘች!

እኔ ለተሰንበት በጣም የምወዳት ሯጭ ነች ። አልማዝ አያናም ብቅ ብላ ጠፋች ! የኢትዮጵያ እስፖርት ፌዴሬሽን መፍረስ ያለበት ድርጅት ነው ።

የኢትዮጵያ ዝርያዎች ግን እጅግ እጅግ አኮሩኝ ። ዞሮ ዞሮ እስፖርት የግለሰብ ችሎታ ነው !! ኤቦ ዬቦ ለሲፋን! ለቃልኪዳን! ለለተሰንበት!

ይህ ሁሉ የእስፖርታችን መዳከም ከጎሳ ፖለቲካ ቀውስ ጋራ እንዳይያያዝ ፈራሁ !!!




Re: ኢትዮጵያ የ10000 ሜትር ወርቅ አጣች! የኢትዮጵያ ዝርያዎች ግን አለምን አስደነቁ !!

Posted: 07 Aug 2021, 10:00
by Horus
በችግር የተከበበው ፌዴሬሽን እና የኦለምፒክ ኮሚቴ

ሰለሞን ባረጋ 5000 እንዳይሮጥ በመከልከሉ አንድ ወርቅ አጥተናል
ሙክታር ኢድሪስ እንዳይሮጥ በመከልከሉ ሌላ ወርቅ አጥተናል


Re: ኢትዮጵያ የ10000 ሜትር ወርቅ አጣች! የኢትዮጵያ ዝርያዎች ግን አለምን አስደነቁ !!

Posted: 07 Aug 2021, 10:39
by Horus
ይህ አሰልጣኝ ተሰማ አስደናቂ ሳይንቲስት ነው ። ለተሰንበት እንዴት እንደ ምትሸነፍ እንደ ሳይንስ ተንብዮት ነበር ! በመጨረሻው 400 ሜትር ላይ ... አስገራሚ ነው። ስለዚህ በትክክል ሰለሞን ባረጋ 5000 ወርቅ ያገኝ ነበር ። ሙክታር ኢድሪስም እንዲሁ !!

Re: ኢትዮጵያ የ10000 ሜትር ወርቅ አጣች! የኢትዮጵያ ዝርያዎች ግን አለምን አስደነቁ !!

Posted: 07 Aug 2021, 11:00
by Fiyameta
This is just amazing! :shock: :shock: