A Conversation between an Amhara and non-Amhara Ethiopians on the war between Tigray & Amhara Regions
Posted: 26 Jul 2021, 08:20
Abi haileTG • 16 hours ago • edited
ኃይልሽ
In case you haven’t paid enough attention for the last three decades, you can’t possibly find a single family that has not been negatively affected by the Tplf thugs.
The intensity of rage going on right now is impossible for the government to control. Everyone is ready to go to the battlefield. The people are saying ENOUGH!! This is not Amara issue or Oromo issue. Every able individual is ready to bury the thugs.
How do you control a wave of Tigreans ready to kill you? You bring your own wave and finish the job for the last time. Nobody can stop this wave.
If the Tigray people are ready to go to ሲኦል in order to destroy Ethiopia, Ethiopia should take all the necessary actions to bring ሲኦል to them.
Admassie Abi • 4 hours ago • edited
ጌታው ራሥ አቢ፡
1. እንደምታውቀው ማንኛውም ሰው አንድን ተግባር ከመፈጸሙ በፊት የድርጊቱን ጥቅምና ጉዳት አነሰም በዛም በህሊናው ይመዝናል ተብሎ ይታሰባል፡፡ ይህ ምዛኔ አንድ ሰው የሚያከናውነውን ተግባር ለመበየን ከሚያግዙት መስፈርቶች በመነሳት በሚበጀው መደምደሚያ ላይ የሚያደርሰውና ያሰበውን ተግባር ለመፈጸምም ሆነ ላለመፈጸም ለውሳኔ የሚያበቃው ነው፡፡ ታዲያ መንግስታትም ሆኑ ተቋማት እንዲሁ ለሚወስዷቸው እርምጃዎች ውሳኔ ላይ የሚደርሱበት መንገድ ከላይ ከተገለጸው የግለሰቦች የአወሳሰን መንገድ የተለየ አይደለምና፤ ከዚህ የተለመደ የመበየኛ ስልት በመነሳት አሁን ሃገራችን ላይ የተለኮሰውን “ሕግ ለማስከበር” የሚል የዳቦ ስም የወጣለት ጦርነት ሚዛን ላይ በማስቀመጥ እነዚህን የሚቀጥሉትን ጥያቄዎች ላንሳ፡፡
ለክርክር ያህል ወያኔ የለየለት ወንጀለኛ ነው፤ “ሕግ ማስከበር” የሚባለውም የአብይ ዘመቻ እውነት እና ከቀና ተልእኮ የመነጨነው ብዬ ልነሳና፡-
1.1 የወያኔ ጥፋቱ በጦርነቱ ከሚያልቁት፣ ከሚሰቃዩትና ከሚዋረዱት ህዝቦቻችን መከራ በላይ ምን ያህል መጥፎ ቢሆን ነው፤ ወያኔን በማጥፋት ሂደት ይሄ ሁሉ ግፍ በወገኖቻችንን ላይ እንዲፈጸምባቸው የፈረድነው?
1.2 የወያኔ ወንጀሉ ምን ያህል ከሃገር በላይ ቢገዝፍ ነው፤ የወያኔ የጥፋቱ ክብደት ምን ያህል ከሃገር ህልውና በላይ ከባድ ቢሆን ነው፤ ወያኔን በማጥፋት ሂደት ኢትዮጵያን ገደል አፋፍ ላይ አድርሰን እየገፈተርናት እያለ ግን ደግሞ ጉዳያችን አልሆን ያለው? ለዚያውም ይሄ ሁሉ እየሆነ ያለው “ ኢትዮጵያ እናቴ፣ ክብሬ፣ ሞገሴ፣ መቀበሪያዬ!” እያልን ደረት በምንደልቀውና ነጋሪት በምነጎስመው “ልዩ” ልጆቿ አማካኝነት መሆኑ፡፡
1.3 ይሄ ከሆነስ ዘንድ ኢትዮጵያ ማለት ያለ ህዝቦቿ ምንድናት? ሃገር ማለትስ? ልብ ይሏል - ሃገር ማለት በቀላል ቋንቋ ህዝብ + ድንበር ነው፡፡
2. ከአማራ ክልል በትግራይ ክልል ላይ የሚነሳውን የርስትና(የመሬት ይገባኛል) የማነት ጥያቄ በተመለከተ፤ የማነት ጥያቄውን ማንሳት ተገቢ ቢሆንም የጥያቄው አነሳስና ጥያቄውን ለመመለስ የተሞከረበት መንገድ ስህተትና በጣም አደገኛ መሆኑን አሁን ያስከተለውን የጥፋት መዘዝ እያየነው እንገኛለን፡፡
2.1 ጥያቄው የተነሳበት መንገድ፡- ክልሎች ህልውናቸውን ያገኙት በህገ መንግስቱ መሰረት ነው፡፡ ክልሎች የተዋቀሩት ደግሞ የህዝብ አሰፋፈር፣ ቋንቋ፣ ማንነት እና ፈቃድ በሚሉ ህገመንግስታዊ መስፈርቶች ላይ በመመስረት ነው፡፡ ስለሆነም ህገመንግስቱ ክልሎችን ከማወቀሩ በፊት በነበሩ ክ/ሀገሮች ውስጥ የነበሩ ህዝቦችን፤ ለምሳሌ ጎንደር፤ በውስጡ አማርኛ ተነጋሪዎች እና የሰፈሩበትን ቦታ፣ ትግርኛ ተናጋሪዎችና የሰፈሩበትን ቦታ፣ አገውኛ ተናጋሪዎችና የሰፈሩበትን ቦታ፣ ቅማንቶችና የሰፈሩበትን ቦታ ከላይ በተጠቀሱት መስፈርቶች መነሻነት ወደ አዲሶቹ ክልሎች እንዲካለሉ ሆነዋል፡፡ በሌላ አባባል ጎንደር (በቀደመው ጊዜ ቤጌምድርና ስሜን የሚባለውን) በክ/ሀገርነቱ ወቅት አማርኛ ተነጋሪ ህዝቦች ብቻ የሰፈሩበት አስተደደር አልነበረም፤ እንዲሁም “አማራ” የሚባል አስተዳደርም አልነበረም፡፡ ስለሆነም በጎንደር ክ/ሀገር ስር ከነበረ አስተደደር ወደ ትግራይ ክልል አስተዳደር የተዛወሩ ትግርኛ ተናጋሪዎች እና የሰፈሩበትን ቦታ፤ ቦታውን ብቻ መርጦ “ድሮ በጎንደር ክ/ሀገር ስር ስለነበረ የአማራው መሬት የአማራው ርስት ነው” ብሎ ጥያቄ ማንሳት ስህተት ነው፡፡ በዚህ በተሳሳተ አመክንዮ መሰረት ጥያቄው የሚቀጥል ከሆነ ጦርነት የማይለኮስበት ክልል አይኖርም፡፡ ለምሳሌ፡- አፋር የሚባል ክልል አይኖርም፡፡ ምክንያቱም ቦታው ከወሎና ከትግራይ ክ/ሀገሮች በተገኘ መሬት የተዋቀረ ስለሆነ፡፡ ቤንሻንጉልና ጉሙዝ የሚባል ክልል አይኖርም፡፡ ምክያቱም ከጎጃምና ወለጋ ክ/ሀገሮች በተገኘ መሬት የተዋቀረ ስለሆነ፡፡ ወዘተ…
2.2 ጥያቄውን ለመመለስ የተሞከረበት መንገድ፡-
ከአማራ ክልል የተነሳው የመሬት ወይንም የርስት ጥያቄ ስህተት እንደሆነ ከላይ ገልጫለሁ፡፡ ይሁን እንጂ የሚነሳ የማንነት ጥያቄ መኖር የለበትም ማለቴ ግን አይደለም፡፡ የማንነት ጥያቄ ማለት በአንድ በተወሰነ ቦታ፤ ለምሳሌ በወልቃይት፤ አብዛኛው ነዋሪ አማርኛ ተናጋሪ ሆኖ በትግራይ ክልል ውስጥ እንዲካተት ተደርጎ ከሆነ ጥያቄው ለማንነቴ ምላሽ በሚሰጠኝ ክልል ውስጥ ልተዳደር የሚል የመብት ጥያቄ ነው፡፡ ይህ ጥያቄ የሚቀርብበት እና እልባት የሚያገኝበት መንገድ ደግሞ በህገመንግስቱ አንቀጽ 48 “የአከላለል ለውጦች” በሚል በተቀመጠው ሰላማዊ አግባብ መሰረት ብቻ መሆን አለበት፡፡
አንቀጹ የሚለው በአጭር ሲገለጽ፡- ጥያቄው ሲነሳ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ክልሎች በስምምነት ይፈጸማል፡፡ መስማማት ካልቻሉ የፈደሬሽን ምክር ቤት ጥያቄው በቀረበለት በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል ይላል ፡፡
ከዚህ ከላይ ከተጠቀሰው ህገመንግስታዊ መንገድ ውጭ የአማራ ክልል አሁን በተያዘው የጦርነት መንገድ ለመፍታት መሞከሩ አደገኛ ስህተት ነው፡፡ አደገኛነቱ ደግሞ ለሌሎች ተመሳሳይ ጥያቄ ለሚኖራቸው ክልሎች “መፍትሄው ጉልበተኛ መሆን ነው!” የሚል የእርስ በርስ የጦርነት አዋጅ ስለሚሆን ነው፡፡
ህገመንግስቱ ለትግራይ እንዲበጅ ሆኖ የተቀረጸ ስለሆነ ዋጋ የለውም የሚባል ከሆነም፤ ስለዚህ መጀመሪያ ህገመንግስቱን በሰላማዊ መንገድ መቀየር ነው፡፡ አለበለዚያ የዚህ ሁሉ ዘመቻ ዳንኪራ ተልእኮው ህግም ድንበርም የማስከበር ሳይሆን የመተላለቅና ዘር የማጥፋት ይሆናል፡፡ ይሄም አያ ተቤው (አያ ተበጀ፡ ተስፋ ስንታየሁ በጻፈው “ጨዋታ-ጦቢያ በእየሩሳሌም” በሚል መጽሐፍ ላይ ያሉ ከጎንደር የፈለሱ ቤተ-እስራኤላዊ ገጸ ባህሪ ናቸው) እግዜርን ሲወቅሱት “አንተ ምናለብህ ቤትህን ሰው እማይደርስበት ቆጥ ላይ ሰቅለህ የተቆጣ በየት አድርጎ ያግኝህ!” እንዳሉት፤ አዳሜ ምን አለበት ግፋ በለው እሚለው ከወላፈኑ ርቆ በሌላው ደም ነው፡፡
The above discussion was from http://awate.com/encdc-expresses-its-su ... 5469672764
ኃይልሽ
In case you haven’t paid enough attention for the last three decades, you can’t possibly find a single family that has not been negatively affected by the Tplf thugs.
The intensity of rage going on right now is impossible for the government to control. Everyone is ready to go to the battlefield. The people are saying ENOUGH!! This is not Amara issue or Oromo issue. Every able individual is ready to bury the thugs.
How do you control a wave of Tigreans ready to kill you? You bring your own wave and finish the job for the last time. Nobody can stop this wave.
If the Tigray people are ready to go to ሲኦል in order to destroy Ethiopia, Ethiopia should take all the necessary actions to bring ሲኦል to them.
Admassie Abi • 4 hours ago • edited
ጌታው ራሥ አቢ፡
1. እንደምታውቀው ማንኛውም ሰው አንድን ተግባር ከመፈጸሙ በፊት የድርጊቱን ጥቅምና ጉዳት አነሰም በዛም በህሊናው ይመዝናል ተብሎ ይታሰባል፡፡ ይህ ምዛኔ አንድ ሰው የሚያከናውነውን ተግባር ለመበየን ከሚያግዙት መስፈርቶች በመነሳት በሚበጀው መደምደሚያ ላይ የሚያደርሰውና ያሰበውን ተግባር ለመፈጸምም ሆነ ላለመፈጸም ለውሳኔ የሚያበቃው ነው፡፡ ታዲያ መንግስታትም ሆኑ ተቋማት እንዲሁ ለሚወስዷቸው እርምጃዎች ውሳኔ ላይ የሚደርሱበት መንገድ ከላይ ከተገለጸው የግለሰቦች የአወሳሰን መንገድ የተለየ አይደለምና፤ ከዚህ የተለመደ የመበየኛ ስልት በመነሳት አሁን ሃገራችን ላይ የተለኮሰውን “ሕግ ለማስከበር” የሚል የዳቦ ስም የወጣለት ጦርነት ሚዛን ላይ በማስቀመጥ እነዚህን የሚቀጥሉትን ጥያቄዎች ላንሳ፡፡
ለክርክር ያህል ወያኔ የለየለት ወንጀለኛ ነው፤ “ሕግ ማስከበር” የሚባለውም የአብይ ዘመቻ እውነት እና ከቀና ተልእኮ የመነጨነው ብዬ ልነሳና፡-
1.1 የወያኔ ጥፋቱ በጦርነቱ ከሚያልቁት፣ ከሚሰቃዩትና ከሚዋረዱት ህዝቦቻችን መከራ በላይ ምን ያህል መጥፎ ቢሆን ነው፤ ወያኔን በማጥፋት ሂደት ይሄ ሁሉ ግፍ በወገኖቻችንን ላይ እንዲፈጸምባቸው የፈረድነው?
1.2 የወያኔ ወንጀሉ ምን ያህል ከሃገር በላይ ቢገዝፍ ነው፤ የወያኔ የጥፋቱ ክብደት ምን ያህል ከሃገር ህልውና በላይ ከባድ ቢሆን ነው፤ ወያኔን በማጥፋት ሂደት ኢትዮጵያን ገደል አፋፍ ላይ አድርሰን እየገፈተርናት እያለ ግን ደግሞ ጉዳያችን አልሆን ያለው? ለዚያውም ይሄ ሁሉ እየሆነ ያለው “ ኢትዮጵያ እናቴ፣ ክብሬ፣ ሞገሴ፣ መቀበሪያዬ!” እያልን ደረት በምንደልቀውና ነጋሪት በምነጎስመው “ልዩ” ልጆቿ አማካኝነት መሆኑ፡፡
1.3 ይሄ ከሆነስ ዘንድ ኢትዮጵያ ማለት ያለ ህዝቦቿ ምንድናት? ሃገር ማለትስ? ልብ ይሏል - ሃገር ማለት በቀላል ቋንቋ ህዝብ + ድንበር ነው፡፡
2. ከአማራ ክልል በትግራይ ክልል ላይ የሚነሳውን የርስትና(የመሬት ይገባኛል) የማነት ጥያቄ በተመለከተ፤ የማነት ጥያቄውን ማንሳት ተገቢ ቢሆንም የጥያቄው አነሳስና ጥያቄውን ለመመለስ የተሞከረበት መንገድ ስህተትና በጣም አደገኛ መሆኑን አሁን ያስከተለውን የጥፋት መዘዝ እያየነው እንገኛለን፡፡
2.1 ጥያቄው የተነሳበት መንገድ፡- ክልሎች ህልውናቸውን ያገኙት በህገ መንግስቱ መሰረት ነው፡፡ ክልሎች የተዋቀሩት ደግሞ የህዝብ አሰፋፈር፣ ቋንቋ፣ ማንነት እና ፈቃድ በሚሉ ህገመንግስታዊ መስፈርቶች ላይ በመመስረት ነው፡፡ ስለሆነም ህገመንግስቱ ክልሎችን ከማወቀሩ በፊት በነበሩ ክ/ሀገሮች ውስጥ የነበሩ ህዝቦችን፤ ለምሳሌ ጎንደር፤ በውስጡ አማርኛ ተነጋሪዎች እና የሰፈሩበትን ቦታ፣ ትግርኛ ተናጋሪዎችና የሰፈሩበትን ቦታ፣ አገውኛ ተናጋሪዎችና የሰፈሩበትን ቦታ፣ ቅማንቶችና የሰፈሩበትን ቦታ ከላይ በተጠቀሱት መስፈርቶች መነሻነት ወደ አዲሶቹ ክልሎች እንዲካለሉ ሆነዋል፡፡ በሌላ አባባል ጎንደር (በቀደመው ጊዜ ቤጌምድርና ስሜን የሚባለውን) በክ/ሀገርነቱ ወቅት አማርኛ ተነጋሪ ህዝቦች ብቻ የሰፈሩበት አስተደደር አልነበረም፤ እንዲሁም “አማራ” የሚባል አስተዳደርም አልነበረም፡፡ ስለሆነም በጎንደር ክ/ሀገር ስር ከነበረ አስተደደር ወደ ትግራይ ክልል አስተዳደር የተዛወሩ ትግርኛ ተናጋሪዎች እና የሰፈሩበትን ቦታ፤ ቦታውን ብቻ መርጦ “ድሮ በጎንደር ክ/ሀገር ስር ስለነበረ የአማራው መሬት የአማራው ርስት ነው” ብሎ ጥያቄ ማንሳት ስህተት ነው፡፡ በዚህ በተሳሳተ አመክንዮ መሰረት ጥያቄው የሚቀጥል ከሆነ ጦርነት የማይለኮስበት ክልል አይኖርም፡፡ ለምሳሌ፡- አፋር የሚባል ክልል አይኖርም፡፡ ምክንያቱም ቦታው ከወሎና ከትግራይ ክ/ሀገሮች በተገኘ መሬት የተዋቀረ ስለሆነ፡፡ ቤንሻንጉልና ጉሙዝ የሚባል ክልል አይኖርም፡፡ ምክያቱም ከጎጃምና ወለጋ ክ/ሀገሮች በተገኘ መሬት የተዋቀረ ስለሆነ፡፡ ወዘተ…
2.2 ጥያቄውን ለመመለስ የተሞከረበት መንገድ፡-
ከአማራ ክልል የተነሳው የመሬት ወይንም የርስት ጥያቄ ስህተት እንደሆነ ከላይ ገልጫለሁ፡፡ ይሁን እንጂ የሚነሳ የማንነት ጥያቄ መኖር የለበትም ማለቴ ግን አይደለም፡፡ የማንነት ጥያቄ ማለት በአንድ በተወሰነ ቦታ፤ ለምሳሌ በወልቃይት፤ አብዛኛው ነዋሪ አማርኛ ተናጋሪ ሆኖ በትግራይ ክልል ውስጥ እንዲካተት ተደርጎ ከሆነ ጥያቄው ለማንነቴ ምላሽ በሚሰጠኝ ክልል ውስጥ ልተዳደር የሚል የመብት ጥያቄ ነው፡፡ ይህ ጥያቄ የሚቀርብበት እና እልባት የሚያገኝበት መንገድ ደግሞ በህገመንግስቱ አንቀጽ 48 “የአከላለል ለውጦች” በሚል በተቀመጠው ሰላማዊ አግባብ መሰረት ብቻ መሆን አለበት፡፡
አንቀጹ የሚለው በአጭር ሲገለጽ፡- ጥያቄው ሲነሳ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ክልሎች በስምምነት ይፈጸማል፡፡ መስማማት ካልቻሉ የፈደሬሽን ምክር ቤት ጥያቄው በቀረበለት በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል ይላል ፡፡
ከዚህ ከላይ ከተጠቀሰው ህገመንግስታዊ መንገድ ውጭ የአማራ ክልል አሁን በተያዘው የጦርነት መንገድ ለመፍታት መሞከሩ አደገኛ ስህተት ነው፡፡ አደገኛነቱ ደግሞ ለሌሎች ተመሳሳይ ጥያቄ ለሚኖራቸው ክልሎች “መፍትሄው ጉልበተኛ መሆን ነው!” የሚል የእርስ በርስ የጦርነት አዋጅ ስለሚሆን ነው፡፡
ህገመንግስቱ ለትግራይ እንዲበጅ ሆኖ የተቀረጸ ስለሆነ ዋጋ የለውም የሚባል ከሆነም፤ ስለዚህ መጀመሪያ ህገመንግስቱን በሰላማዊ መንገድ መቀየር ነው፡፡ አለበለዚያ የዚህ ሁሉ ዘመቻ ዳንኪራ ተልእኮው ህግም ድንበርም የማስከበር ሳይሆን የመተላለቅና ዘር የማጥፋት ይሆናል፡፡ ይሄም አያ ተቤው (አያ ተበጀ፡ ተስፋ ስንታየሁ በጻፈው “ጨዋታ-ጦቢያ በእየሩሳሌም” በሚል መጽሐፍ ላይ ያሉ ከጎንደር የፈለሱ ቤተ-እስራኤላዊ ገጸ ባህሪ ናቸው) እግዜርን ሲወቅሱት “አንተ ምናለብህ ቤትህን ሰው እማይደርስበት ቆጥ ላይ ሰቅለህ የተቆጣ በየት አድርጎ ያግኝህ!” እንዳሉት፤ አዳሜ ምን አለበት ግፋ በለው እሚለው ከወላፈኑ ርቆ በሌላው ደም ነው፡፡
The above discussion was from http://awate.com/encdc-expresses-its-su ... 5469672764