Page 1 of 1

ህወሃት እርስ በርሷ ልትበላላ ጫፍ ደርሳለች!!! “አማራው ጌታቸው ረዳ ትግራይን አይመራም” በረኸኞቹ ትህነጎች

Posted: 14 Jul 2021, 18:03
by Wedi
ህወሃት እርስ በርሷ ልትበላላ ጫፍ ደርሳለች!!! “አማራው ጌታቸው ረዳ ትግራይን አይመራም” በረኸኞቹ ትህነጎች



ህወሃት እርስ በርሷ ልትበላላ ጫፍ ደርሳለች!!! “አማራው ጌታቸው ረዳ ትግራይን አይመራም” በረኸኞቹ ትህነጎች

“አማራው ጌታቸው ረዳ ትግራይን አይመራም” በረኸኞቹ ትህነጎች


በተከታታይ በቲውተር ገጹ መረጃ የሚያሰራጨው የአሸባሪው ትህነግ አባል ጌታቸው ረዳ ትግራይን እንደማይመራ ክርክር ተነስቷል።

የራያ ልጅ የሆነውና ፍጹም የአማራ ደም ያለው ባንዳው ጌታቸው ቀደም ሲል በዩኒቨርስቲ መምህርነቱ ወቅት በረኸኞቹን ትህነጎች “ህግ የማያውቁ፣ ደደቦች፤ ምንም የማይገባቸው፤ መሃይም ደናቁርት” እያለ ክፍል ውስጥ ሲያንኳስስ እንደ ነበር የሚናገሩት ተማሪዎቹ የትህነግ አባል መሆኑ ይፋ ከሆነ ማግስት ጀምሮ ግን ለትህነግ አጎብዳጅና ተገዢ እየሆነ መምጣቱን እነዚሁ ተማሪዎችና በቅርብ የሚውቁት ይመሰክራሉ።

“እዳ በዝቶበት መክፈል ሲያቅተው የትህነግ አባል ሆኖ ማገልገል ጀመረ፤ ለፕሮጀክት የተሰጠውን ገንዘብ ሙልጭ አድርጎ በላው፤ ወሰበበት፣ ጠጣበት፤ ትህነጎችም በስልት አበሰበሱት” ሲሉ ጌታቸውን በቅርብ የሚውቁት ይናገራሉ። በቀጣይም “ዕዳ ስረዛ ተደርጎለት ትህነግን በነውሩ እንዲቀላቀል ተደረገ” ሲሉ እነዚሁ ወገኖ ያስረዳሉ።

ከለውጡ በኋላ ዋና ተዋናይ በመሆን ፊት የተቀመጠው ራያው ጌታቸው ረዳ ከህግ ማስከበሩ ዱላ ተርፎ በበረኻ ከአውሬ ጉድጓድ ብቅ እያለ በሚሰጠው ማብራሪያና በሚያሰራጨው መረጃ በትህነግ ደጋፊዎች ዘንዳ ታዋቂና ስሙ በሚዲያ የሚጠራ “አዲስ ታጋይ” ሊሆን ችሏል።

በጦርነቱ በርካታ የትህነግ ነባርና የመካከለኛ ዕድሜ አመራሮች መገደላቸውን ተከትሎ ግንባር ቀደም የሆነው ጌታቸው ትህነግ ከጉድጓድ ወደ መቀሌ ከገባ በኋላ “ትግራይን መምራትም ሆነ መወከል አይችልም፣ አማራ ነው” የሚሉ የትግራይ ሰዎች በዝተዋል።

በአማራነቱና በቀድሞው የትህነግ የበረኻ ትግል ተጋዳላይ ያልነበረ በመሆኑ ከትህነግ አመራሮች ውስጥ የተለየ እንደሆነ የሚነገርለት ጌታቸው፤ የአሸባሪው ትህነግ የነፍስ አባት ስብሃት ነጋ እጅግ ይዘልፈውና ይንቀው እንደነበር፣ እንዲያውም በአንዳንድ ላይ ጌታቸው ሃሳብ ሲሰጥ ስብሃት ማንነቱን እየጠቀሰ “ዝም በል አንተ …” ይለው እንደነበር ከራሱ ከትህነግ የወጡ መናገራቸው አይዘነጋም።

በዚህ በቆየው የማንነት ቀውስ ይሁን በሌላ በግልጽ ባይነገረም ጌታቸውን አስመልክቶ የተለያዩ አመለካከት መያዙን የኢትዮ12 የአዲስ አበባ ተባባሪ ዘግቧል። እሱ እንዳለው ጌታቸው ክልሉ ቃለ አቀባይነት የዘለለ ኃላፊነት ከተሰጠው ቅቡል አይሆንም። ሰሞኑንን ድርድር አስመልክቶ የተለያየ አቋም መያዙን እንደሰሙ ለትህነግ ቅርብ የሆኑ እየገለጹ ነው።

በሰሜን አሜሪካ የሚኖረውና ለትህነግ የውጭ ክንፍ አመራሮች ቅርብ ሰው ባልደረባ ሰማሁ እንዳለው የጌታቸው ገኖ መውጣት አሁን አሁን ቅሬታ እንዲሰነዘርበት እያደረገ ነው። እሱ እንደሚለው አዲስ ቃል አቀባይ ሁሉ ሊሾም ይችላል። “ጌታቸው በየደቂቃው ትዊት የሚያደርገው የውስጥ የበላይነት ለመያዝና በውጭ ያለውን የትህነግ የጀርባ አጥንት ለመያዝ ነው” የሚሉ በተመሰቃቀለውና በተበታተነው ትህነግ ውስጥ በቅርቡ “ሽኩቻ እንሰማለን” ባይ ናቸው። ሽኩቻ ብቻ ሳይሆን ምን አላባትም “የጦር አበጋዝነት ክፍፍል ትግራይ እንደሚገጥማት እሙን ነው” የሚሉም እየተነሱ ነው።

ሌላው የወንበዴው ትህነግ መሪ ሆኖ ለመውጣት እየታተረ ያለው ጻድቃን ገብረትንሳይ ከማይታወቅ ቦታ ሆኖ መግለጫ መስጠቱ፤ በህይወት አሉ የሚባሉት መተንፈስ መጀመራቸውና ሁሉም ተሰባስበው አንድ ላይ አመራር አለመጀመራቸው ይታወቃል። ከዚህ አኳያ ትህነግ እንደ ቡድን ወጥ አመራር ይዞ በአንድ መሪ ብቅ ለማለት አለመቻሉ ከበፊት ጀምሮ በትህነግ ውስጥ ያለውን የጎጥ ክፍፍል እያባሰው እንደሄደ ይነገራል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ “አማራው ጌታቸው” የትግራይ አዲስ ትውልድ መሪ ሆኖ ብቅ ለማለት መፈለግ ከማንነቱ ጀምሮ በጽንፈኛ ትህነጎች ዘንድ ተወዳጅነትን አላተረፈለትም። ትህነግ እንዳበቃላትና በነጌታቸው ዓይነት “አዲስ ትህነጎች” መመራት አለባት የሚሉቱ ከጽንፈኞቹ ጋር ፍጥጫ ውስጥ ገብተዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የአድዋ የበላይነትን ለማስጠበቅ የሚጥሩት ጥቂት ርዝራዦች ከሁለቱም ጋር በሌላ ጽንፍ ተያይዘዋል።

በትግራይ አውራጃ እየተለየ የሚፈጸመው ግድያ የከፋ መሆኑ፣ ወደ ኤርትራ የሚሰደዱ መኖራቸው፣ ጉዳዩን የዓለም ዓቀፉ ህብረተሰብ እንዲከታተለው መጠየቁ እያደር ነገሮች ሲጠሩ “ማን የማንን አካባቢ አጠቃ” የሚለው የልዩነቱ መሰረታዊ ማጠንጠኛ እንደሚሆን አስተያየት የሚሰጡ፣ ትላንት ዶ/ር አብርሃምና የራዩማ ፓርቲ አመራር እንዳሉት በራያ ከሰላሳ ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው የጉዳዩን አሳሳቢነት ያሳያል።

ነገሩን ከዳር ሆነው ለሚያዩ አማራው ጌታቸው በትግራይ መሪ ሊሆን እንደማይችል ያምናሉ። ሆኖም ጌታቸው ከአብን የተወሰኑ አመራሮች ጋር ግንኙነት እንዳለው እናውቃለን የሚሉ ግን ግምታቸው ሌላ ነው። (ከኢትዮ12 የተቀናበረ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Re: ህወሃት እርስ በርሷ ልትበላላ ጫፍ ደርሳለች!!! “አማራው ጌታቸው ረዳ ትግራይን አይመራም” በረኸኞቹ ትህነጎች

Posted: 14 Jul 2021, 18:11
by TesfaNews
His dad is Chigreway:lol: :lol: