Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11590
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

የትግራይ ህዝብ ተወሯል – ሳልሳይ ወያነ ትግራይ

Post by sarcasm » 28 Apr 2021, 08:46

እኛም በአዲሱ የትግል ምእራፍ ላይ እንገኛለን ሲሉ የሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ምክትል ሊቀመንበር አቶ አሉላ ሀይሉ ተናግረዋል፡፡

ምክትል ሊቀመንበሩ አከሎም እንደ ትግል ቆጥረን አዲስ የዲፕሎማሲ ስራዎች እየሰራን ነውም ብለዋል፡፡

እንደ ፓርቲ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በመሆን ህዝቡ እያጋጣመዉ ካለዉ ችግር እንዲወጣ ሰላማዊ ትግል እያደረግን ነዉም ብለዋል ምክትል ሊቀ መንበሩ፡፡

በትግራይ ክልል ያለዉ ጦርነት ሕዝባዊ ትግል ሆነዋል ያሉት አቶ አሉላ የትግራይ ህዝብ እየደረሰበት ያለዉ ግፍ የአለም ማህበረሰብ እንዲያቀዉና የሰብአዊ እርዳታ እንዲያገኝ እንዲሁም ሚድያዎች በህዝቡ ላይ እየደረሰ ያለዉን ግፍ እንዲዘግቡ የማስተባበር ስራ እየሰሩ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ትግራይ ከወራሪ ሀይሎች ነጻ እስክተወጣ እና የትግራይ ህዝብ የመረጠዉ መንግስት እስኪ መራው እንደ ፓርቲ ሆነ እንደ ግለሰብም እየሰራን ነዉ ብለዋል፡፡

Continue reading