Page 1 of 1

"በህወሓት የተነገሩ ሁሉም መሬት ላይ ተፈፀሙ....በቃን............ህወሓት አለማመናችን ልክ አልነበርም" - ኑዛዜ - ተፃፈ በሚኪ ተስፋይ ( የፈንቅል ትግራይ አመራር)

Posted: 26 Apr 2021, 07:53
by sarcasm
ተፃፈ በሚኪ ተስፋይ ( የፈንቅል ትግራይ አመራር)

¤ ህወሓት እና የትግራይ ህዝብ አንድ አልነበሩም ።።።።
ህወሓት እና የትግራይ ህዝብ አንድ አልነበሩም አሁን በመሬት ላይ ያለው ሐቅ ግን
ከአንድ በላይ አንድ ሁነዋል በአካል : በስጋ :በመንፈስ በራሃብ በጥም በሞት በስቃይ አንድ ሁነዋል።
በዳይ ከተበዳይ ይቀራረባል ዛሬ ህወሓት እና የትግራይ ህዝብ አንድ ናቸው ።
`ዛሬ እንደ ትናትና ደብረፅዮን : ጌታቸው ረዳ; መያዝ አለመያዝ አይደለም። ይህንን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊገነዘበው ይገባል። ጌታቸው ረዳ ደብረፅዮን ቢያዝ ባያዝ ትግራይ ምድር መሬት ላይ ያለው እውነታ ምንም የሚቀይረው ነገር የለም።

"""""""" እንዴት እና ለምን ለሚል ሰው """""""""""

"በ3 ሳምንት ያለቀው ጦርነት ለምን 5ኛው ወር ድረስ እንዲራዘም ሆነ ብሎ የሚጠይቅ ሰው ካለ መልሱ በጣም ቀላል ነው።
"እኔ ህወሓት ወደ ጦርነት ከገባ በ3 ቀን ህወሓት ይደመሰሳል የሚል 100% እምነት ነበረኝ ። ጦርነቱ ከተጀመረ < ሳይጀመር ያለቀ ጦርነት >ነው ብዬ ረጅም ፅሁፍ ፅፌ ነበር ። አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን በተቃራኒ ነበር የህወሓት ሃይል ሲገምተው የነበረው ከባድ እንደሆነ ነበር ይህንንም ልክ ነበር ምክንያቱም የህወሓት ሰልፍ የህወሓት በድምፅ ወያነ ንግግር የትግራይ ህዝብ አድርጎ ወስዶት ስለ ነበረ። የእኔና የተወሰኑ ተጋሩ ግምት ህወሓት ብቻው ነው ህዝብ የለውም የሱ ካድሬዎችም አያምኑትም የሚል ነበር።

የእኔና የተወሰኑ የትግል ጓዶች እውነት ነበር (በ3 ሳምንት አለቀ ) የብዙዎች ኢትዮጵያውያን ግምት ግን ህወሓት እና የትግራይ ህዝብ አንድ ሁኖዋል የሚል ነበር። መጀመርያ ስህተት ነበር ። አንድ እንዳልሆነ መሬት ላይ ተረጋገጠ።

ዛሬ ነው የትግራይ ህዝብ እና ህወሓት አንድ ናቸው ማለት ያለብን።

የህወሓት ከፍተኛ አመራር የዶ/ር ደብረፅዮን እና የጌታቸው ረዳ ምስል ይጋራሉ። የትግራይ ህዝብ ከዚህ በባሰ መሬት ላይ ወድቆ በራሃብ : በስደት :ለቤት አልባ በከባድ ስቃይ ወድቆ ይገኛል ። ዛሬ የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጀነራሎች ኮነሬሎች እኩል ከትግራይ ህዝብ ቆሎ ቂጣ እየበሉ ያድራሉ ይውላሉ እስዋም ካገኝዋት ነው ለ3 ቀን ቆሎ ቂጣ ምንም ሳይበሉም የሚቆዩበት ሁኔታ እንዳለም መረጃው ያመለክታል ።

(((((( ***** የትግራይ ህዝብ ወደ ህወሓት እንዴት ተቀላቀለ እንዴት አንድ ሆነ ለምትሉኝ *****)))))))

¤ የህወሓት የዓልዓሳ (ደጉዓ ተንቤን ) ምሽጉ ከተሰበረ በኋላ..
¤ የህወሓት የጨርጨር (ራያ) ምሽጉ ከተደረመሰ በሆላ
የህወሓት የወርቃምባ (ቆላ ተንቤን) ምሽጉ ከተደረመሰ በኋላ
¤ የህወሓት የሕሞራ (ወልቃየት ሕሞራ) ምሽጉ ከተሰበረ በኋላ...
ህወሓት ለብቻው ከትግራይ ህዝብ ተነጥሎ በ3 ሳምንት ብትንትኑ ወጥተዋል ። ልዩ ሃይሎም ወደ ቤቱ ተመለሰ ተበታተነ (ምክራችን የሰሙ ልዩ ሃይሎች ብዙ ነበሩና) ኦሮማይ ግጥምያው በኢትዮጵያ ሰራዊት በኤርትራ ሰራዊት በድሮን ድል ተጠናቀቀ።

((((((((#ካዛ ምን ተፈጠረ )))))

1ኛ የአማራ ተስፋፊ ሃይል መሬቴን መለስኩኝ ርስቴን ወሰድኩኝ አለ በደም የተወሰደ በደሜን መልስኩኝ ተባለ..!

2ኛ የአማራ ተስፋፊ ሃይል ትግሬ ውጣ ከተከዜ መላሽ ነው ቤትህ አለ ትግራዋይ በግፍ ተባረረ ንብረቱ ተነጠቀ ቤቱ ተወረሰ ተደፈረ ልጆቹ ተደፈሩ ተዋረዱ .... !
3ኛ በመከላከያ ውስጥ የነበሩ አሸንፈናል ከእንግዲህ ብለው ያሰቡ ድኩማን የትግራይ ሃብት መውረር ጀመሩ

መኪና መጫን ጀመሩ ወጣቱ ማንቃሸሽ ጀመሩ ሽኮር መቸርቸር ጀመሩ ለወጣቱ ጁንታ እያሉ ማንቋሸሽ ጀመሩ አሸናፊ ተሸናፊ ተፈጠረ....!

4ኛ ከ1.2 ሚሊዮን ትግራዋይ ተፈናቀለ ወደ አዳባባይ ተበተነ ቀጠለ እንዲህ እንዲህ እያለ 10/15 ቀን ቆየ ዛሬ ነገ ይስተካከላል ብሎ ህዝቡ ዝም ብሎ መከታተል ጀመረ...!

5ኛ ወጣት እየሰበሰቡ በሓወዜን በተንቤን በዕዳጋ ዓርቢ መረሸን ተጀመረ ። በልዩ ሃይል ጥቃት የደረሰበት መከላከያ (ሁሉም አላልኩም) በንዴት በንፁሃን ተጋሩ ደም መመለስ ተያያዙት.....!

6ኛ መከላከያ የግል ተሽከርካሪ የህዝብ ተሽከርካሪ በጦርነት ተገኝቷዋል በሚል ተልካሻ ምክንያት ፍርድ እስኪ ሰጣቸው አንሰጥም የሚል መልስ ተሰጠው... !
7ኛ በጠራራ ፀሃይ የህዝብ ንብረት እየተዘረፉ ወደ አማራ መንግሰት እጅ ገቡ ። የህዝብ የግል መኪና ማሽነሪ ተዘርፈው ወደ አማራ መንግሰት እጅ እንዲገቡ በአማራ መንግሰት ተቋም እንዲሰማሩ ተደረጉ። ይህም የትግራይ ህዝብ በፅሞና ይከታተል ነበር ።

8ኛ ራያ አላማጣ መኾኒ ኮረም ወዘተ የአማራ ነው ተባለ ማንም ድርሽ አይለም ተባለ ብዙ ተጋሩ ነን ያሉ የራያ ተወላጆች በአማራ ልዩ ሃይል እና ምልሻ ተንቆሻሹ ተደበደቡ ለእስር ተዳረጉ የሚገደሉም ተገደሉ መታወቅያም በአማራ ተሰጡ ። ትምህርት ቤት አላማጣ ተጀመረ በአማረኛ😀 ይህ ሁሉ የሚሆነው በሽፍታው የአማራ መንግሰት ነበር ።

9ኛ በትግራይ ህዝብ የደረሱ ግፎች ወደ ጎን በመተው የኢትዮጵያ ሚድያወች የትግራይ ግፍና በደል መፈናቀል እና ሞት አፍነው በመከላከያ ብቻ የደረሰው ግፍ ብቻ መዘገብ ጀመሩ (መልካም ነው መዘገባቸው ነገር ግን ስለ ተፈናቀለው ስለ ሞተው ስለ ተዘረፈ ስለ ተገደለ ትግራዋይ ታፈነ አንዲት ድምፅ ጠፋች። ስለ የተደፈረች ሴት ትግራወይቲ አዶ ትግራወይቲ ፍፁም ድምፅ የሚያሰማ ጠፋ።

10ኛ ስለ ዕዳጋ ሓሙስ ቤተ ክርስተያን ውስጥ 120 የሚደርሱ ንፁሃን ተጋሩ የተረሸኑ ምንም አልተባለም ዝም ጭጭ ተባለ።

11ኛ ስለ አክሱም ጭፍጨፋ ዝም ጭጭ ተባለ አንድም የሚናገር ጠፋ በአይኑ ያየ መስፍን ደሳለኝ በመረጃ ቲቪ የተናገረ ሰውም ለምን ትናገራለህ ተብሎ ከግዝያዊ መስተዳደር እንዲገለል ተደረገ ።

13ኛ በተንቤን በአንድ ቀን ከ140 ሰው ንፁሃን ዜጎች የተረሸኑ የሚናገር የሚተነፍስ ጠፋ ። የንፁሃን ደም መጮሇ ጀመረ .... !

14ኛ ስለ ትግራይ ህዝብ መፈናቀል መገደል መሞት ራሃብ ችግር ስደት ፍልሰት ስለ ትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ስለ የኤርትራ መንግሰት ጥፋት መግለጫ የሰጠ ዓረና ለምን በትግራይ ቲቪ ተላለፈ ተብሎ ዓምዶም ገብረስላሴ ከግዝያዊ መስተዳደር ተባረረ አብርሃ ደስታም ሊያሸማቅቁት ተሞኮረ ወዘተ ..... !

15ኛ የትግራይ ንብረት የሆኑ መመለስ አለባቸው ስለ ኢንጅነር አሉላ የትግራይ ኮንስትሬክሽን ቢሮ ሃላፊ ለምን እንደዚህ አልክ ተብሎ ከስልጣኑ ተባረረ ወዘተ.....!

የትግራይ ህዝብ ይህንን ሀሉ ሲሆን ዝም ብሎ ተመለከተ አየ አስተዋለ.... አንድ መንግሰት ሲወድቅ እንደዚህ ነው እስኪ እንታገስ የሚል ትግራዋይ ሁሉም

ፊቱ መጥቆር ጀመረ...
አይኑ መቅላት ጀመረ...
መከላከያ በአይን ቁራኛ መመልከት ጀመረ...
አማራ ተስፋፊ ወሪራ መሬት መሆኑ ተመለከተ..
ዶ/ር አብይ በደል ማስቆም የማይችል መሆኑ ተመለከተ...
በህወሓት የተነገሩ ሁሉም መሬት ላይ ተፈፀሙ....
በቃን............ህወሓት አለማመናችን ልክ አልነበርም ።


ህወሓት እና የትግራይ ህዝብ አንድ ናቸው እንዳሉን እኛም አንድ ነን የሚል አቋም ወሰደ ዛሬ የትግራይ ህዝብ ከደብረፅዮን መያዝ አለመያዝ ከጌታቸው ረዳ መያዝ አለመያዝ የሚገናኝ ትግል የለውም ። የትግራይ ወጣት እንደ ቅጠል እየረገፈ ቢሆንም በትግራይ ህዝብ እየደረሱ ያሉ ግፎች እስካልቆም በረሃ ላይ ሊገናኙ ይችላሉ................ !!

መፍትሄ ምን ይሁን ለምትሉ ...... !

ከላይ የተጠቀሱ የተቀመጡ የተባላሹ ተግባር መታረም መስተካከል አለባቸው የተዘረፉ ንብረቶች መመለስ አለባቸው የተፈናቀለው ህዝብ ወደ ቤቱ ይመለስ ።

ካልሆነ ህወሓት እና የትግራይ ህዝብ አንድ ሆነዋል መለየት አይቻልም!!

Miki tesfay

https://www.facebook.com/isaac.welday.9 ... 6268537607

Re: "በህወሓት የተነገሩ ሁሉም መሬት ላይ ተፈፀሙ....በቃን............ህወሓት አለማመናችን ልክ አልነበርም" - ኑዛዜ - ተፃፈ በሚኪ ተስፋይ ( የፈንቅል ትግራይ አመራር)

Posted: 26 Apr 2021, 09:31
by Fed_Up
^^^

አታላዝንብን!! "የአጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል" ይላሉ ጌቶችህ ሲተርቱ:: የስልጣን ጥመኞች እነ ፈንቅል ቢሞት ስልጣን አይዙም:: አራት ነጥብ:: ትግራይ ወደድሽም ጠላሽም ተረግጠሽ ወይ አምነሽ ትገዣለሽ:: ሌባ ሁላ

Re: "በህወሓት የተነገሩ ሁሉም መሬት ላይ ተፈፀሙ....በቃን............ህወሓት አለማመናችን ልክ አልነበርም" - ኑዛዜ - ተፃፈ በሚኪ ተስፋይ ( የፈንቅል ትግራይ አመራር)

Posted: 26 Apr 2021, 10:57
by Abere
sarcasm,

ለምን ቢያንስ ከዛሬ ፩፭ ዓመት በፊት እንደዚህ አትፅፍም ነበር ወይስ ያኔ ዐይኖ ህ በጥቁር ጨርቅ ወየኔ ሸፍኖት ነበር።

ወትሮ ነበር እንጅ መጥኖ መደቆስ ፣
አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ።

በመሰረቱ ማንም አማራ ሌሎች ኢትዮጵያዊያምን ትግሬን አይጠሉም ፤ ወያኔን ግን እጅግ ተፀይፈው ይጠላሉ። ምክንያቱ ደግሞ የግፉ መአት ነው። ግፍ የሰራ ደግሞ ትግሬ ይሁን አመራ ጉራጌ ይሁን ኣኦሮሞ ጥቁር ይሁን ነጭ ይጠላል - ስለ ወንጀሉ ይሳደዳል። ወያኔን መጥላት ትግሬን መጥላት አይደለም። ትግሬ እና ወያኔ በመደባለቅ ቁማር ለመጫዎት ከሆነ ጩኸቱ ከፍ ብሎ ይቀጥል ግን ማንም አይሰማውም። አማራ ሲቃውም ይሁን ሲደግፍ በምክንያት ነው - መሪ አማራ ስለሆነ አይደግፍም ኦሮሞ ወይም ትግሬ ስለሆነ አልተቃወመም። ለምሣሌ ብዙ አማራ ለምን ለማ መገርሣ ጠቅላይ ሚንስተር አልሆነም ብለው የዐብይን መመረጥ ብዙ ኢ-ፍትሃዊ አይደለም በለዋል። ተመልክት ለማ መገርሣ ብዙ ኦሮሞ ይመስላል ለማ ግን የድሞግራፊ ለውጥ ፊታውራሪ ነበር። በመቀጠል የወያኔ ህዋስ /ሴል/ ከመስረቱት ሰባቱ ግለሰቦች አንዱ አማራ ነበር ግን ስሙ እንደ ሰብዓ ሰገል ብግልጽ አይነገርም ምክኛቱም ትግሬ አይደለም እምበር ተገዳላይ ተብሎ መጠራት የለብትም። ተላለው አማራ የትግራይ ህዝብ ተጨቁኗል መላው የኢትዮዽያ ህዝብ አማራውን ጨምሮ ተጨቁኗል በሚል ነው። አሁን በህይወት ቢኖር እንደት ንስሃ በገባ ነበር የ 7 ሚልዮን አማራ ህይወት በወያኔ ዘር ማጽዳት ፕሮጀክት ሲቀጠፍ። ስለዚህ የለበጣ ሳይሆን ሰው ማለት የእውነት ዕምባ የሚያፈስ ነው። የውሼት ለቅሶ የምር ለቅሶ ያመጣል።

Re: "በህወሓት የተነገሩ ሁሉም መሬት ላይ ተፈፀሙ....በቃን............ህወሓት አለማመናችን ልክ አልነበርም" - ኑዛዜ - ተፃፈ በሚኪ ተስፋይ ( የፈንቅል ትግራይ አመራር)

Posted: 26 Apr 2021, 12:37
by Axumezana
It is never late to see the truth and change ! I hope Abiy will also see this fact and get ready to negotiate with the victorious TPLF. TPLF is like the tortoise and the protection of the tortoise shell are the Tigray people. As the tortoise lives more than 100 to 200 years, TPLF shall live as far as it remains with the Tigray people.

Re: "በህወሓት የተነገሩ ሁሉም መሬት ላይ ተፈፀሙ....በቃን............ህወሓት አለማመናችን ልክ አልነበርም" - ኑዛዜ - ተፃፈ በሚኪ ተስፋይ ( የፈንቅል ትግራይ አመራር)

Posted: 26 Apr 2021, 12:48
by Abere
The problem is not Abiy Ahmed, the problem is TPLF is an out dated and out of mode tribal mind. It has been useless and will have no usefulness. Let alone Abiy Ahmed, now fighting for his seat, no earthly power can breath life into TPLF's nostrils. It is dead. Really, on what kind of Amhara back will TPLF sailed across the Amhara territory (land of the braves) to Emperor Menelik II palace just like the 1990s ድንጋይ ዳቦ በነበረበት ዘመን. Now, now Weleqait or Humera, or Raya people feed TPLFጤፍ እንጀራ በእርጎ rather TPLF will get their bullets' instead.
Axumezana wrote:
26 Apr 2021, 12:37
It is never late to see the truth and change ! I hope Abiy will also see this fact and get ready to negotiate with the victorious TPLF. TPLF is like the tortoise and the protection of the tortoise shell are the Tigray people. As the tortoise lives more than 100 to 200 years, TPLF shall live as far as it remains with the Tigray people.