Page 1 of 1

Is the Somali's kilil president bipolar? ምንም ሊገባኝ አልቻለም

Posted: 10 Apr 2021, 10:41
by Abaymado
በመጀመርያ ደረጃ እዚህ አገር በጣም ተቀባይነትን ካገኘ ሰው መካከል አንዱ መስጠፌ( ተሳስቼ ይሆን?) ነው:: ጠቅላይ ሚንስትር ቢሆን የሚለው ሕዝብ ቁጥር የትየለሌ ነው:: ስለአማራ በመቆርቆር የሚናገራቸው ነገሮች በሕዝቡ ዘንድ ትልቅ ቦታን እንዲያገኝ አስችሎታል:: አብይ እና እሱ ቢወዳደሩ የሚያሸንፍ ይመስለኛል:: ብቻ የዚህ ሰው አጨራረሱን ማየት ነው:: አደጋ ላይ እንዳይወድቅ እሰጋለሁ::

ከሁሉም በላይ ያ የሲኦል ምድር የነበረውን የሶማሊ ክልል የተረጋጋ ማረጉ በጣም አሳገራሚው ነው:: ለምን ኦሮምያ እንዲህ አልሆነም? የአብይ ስህተት ይመስለኛል:: መሪው አመራረጡ አለ ወይም ከራሱ አብይ ችግር አለ::

ወደ ዋናው ጉዳይ ስገባ :

የሚናገራቸውና የሚሰራቸው ነገሮች የተመታታ ሆነብኝ:: በጣም ለሚርቀው አማራ ሲቆርወቆር የሚቀርበውን አፋርን ግን መግደልና ማዋረድ ለምን ፈለገ?
እኔ እሱ በብሄረሰብ የሚያምን አልመሰለኝም ነበር: እና በማይረባ መሬት ለምን በመቶ የሚቆጠር ሕዝብ ያልቃል?