"ዶጋሊ የኤርትራ ክፍል በመሆኗ የዶጋሊ ድልን ማክበር እንዳቆምነውና ራስ አሉላንም አብረን መዘከር እንዳቆምነው ሁሉ ዓድዋንም ላንዘክር የምንችልበት ጊዜ ይመጣል።" ያሬድ ሹመቴ «ጉዞ ዓድዋ»
Posted: 16 Mar 2021, 08:52
አቶ ያሬድ ሹመቴ የ«ጉዞ ዓድዋ» አስተባባሪ ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ፦
አስተባባሪዎቹ ከአላማጣ ተነስተን መቀሌን አልፈን እስከ ውቅሮና አካባቢው ያለውን ሁኔታ ለመገንዘብ ሞክረናል። ያየነው ችግር በእኛ እምነት፣ በኢትዮጵያ ለዘመናትና ለትውልድ የሚተርፍ ቁርሾ እንዳያፈራ የሚያሰጋ፣ የስነ-ልቦና ጉዳት መድረሱን አስተውለናል። እናም የትግራይ ህዝብ አሁን ባለበትና በተያዘው መንገድ የሚ'ተውና በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ፣ ሁኔታው እስከ ዛሬ በተያዘው የብሽሽቅ መንገድ ከቀጠለ … ምናልባትም ምን ይሆናል መሰለሽ? ዶጋሊ የኤርትራ ክፍል በመሆኗ የዶጋሊ ድልን ማክበር እንዳቆምነውና ራስ አሉላንም አብረን መዘከር እንዳቆምነው ሁሉ ዓድዋንም ላንዘክር የምንችልበት ጊዜ ይመጣል።
* * * * *
እያንዳንዱ ቦታ ላይ ያስተዋልነውና ያየነው ነገር በሁለት መንገድ የተወጠረ ነው። ከውጪ ያለውና የትግራይን ጉዳይ አንስቶ የሚሟገተው አካል የያዘበት መንገድና መንግስት ጉዳዩን የያዘበት መንገድ ከፍተኛ ውጥረት ያለበት ነው። መሀል ላይ ያለውን ህዝብ ስታይው ግን ከፍተኛ የስነ-ልቦና ጉዳት ላይ መውደቁን ትረጂያለሽ። ከፍተኛ ውድመት የደረሰበት፣ የተዘረፉ ቤቶች፣ የተሰባበሩ እቃዎች ፣ በጥይት የተበሳሱ መስታዎቶች፣ የተዘረፉና ኦና የቀሩ ቤቶችን አይተናል።
* * * * *
በሌላ በኩል፤ ህዝቡን ለማናገር ሞክረን ነበር። እኛንም ይቀበሉን የነበሩ ሰዎች ጋር ለመነጋገር እንደሞከርነው ኢትዮጵያዊነታቸው ላይ ጥያቄ ምልክት እንደፈጠረባቸውና የስነ-ልቦና ጉዳት እንደደረሰባቸው አስተውለናል። በምን ምክንያት ይህ ጉዳት ደረሰባቸው ብትይኝ እኔ ልተነትነው አልችልም። መልሱ ፖለቲካዊ ሊሆን ይችላል። ግን በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብ ሰላም አግኝቷል ብሎ ተረጋግቶ መቀመጥ እንደ ሀገር ዋጋ ያስከፍለናል።
* * * * *
የትግራይን ጉዳይ በአዳዲስ መንገዶችና የመፍትሄ ሀሳቦች፣ እስከዛሬ ባልተካሄደበት አዲስ መንገድ ሰላም መፈጠር አለበት። ይሄንን ከእኛ ውጪ ያሉ ምሁራን፣ ፖለቲከኞችም ሆኑ ማህበራዊ አንቂዎች ቆም ብለው ማሰብ አለባቸው። በምንም ተባለ በምንም ህዝቡ ከደረሰበት የህይወት ጫና፣ የስነ-ልቦና ስብራትና ምስቅልቅል መውጣት አለበት።
https://www.facebook.com/getu26/posts/5479434145430115
አስተባባሪዎቹ ከአላማጣ ተነስተን መቀሌን አልፈን እስከ ውቅሮና አካባቢው ያለውን ሁኔታ ለመገንዘብ ሞክረናል። ያየነው ችግር በእኛ እምነት፣ በኢትዮጵያ ለዘመናትና ለትውልድ የሚተርፍ ቁርሾ እንዳያፈራ የሚያሰጋ፣ የስነ-ልቦና ጉዳት መድረሱን አስተውለናል። እናም የትግራይ ህዝብ አሁን ባለበትና በተያዘው መንገድ የሚ'ተውና በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ፣ ሁኔታው እስከ ዛሬ በተያዘው የብሽሽቅ መንገድ ከቀጠለ … ምናልባትም ምን ይሆናል መሰለሽ? ዶጋሊ የኤርትራ ክፍል በመሆኗ የዶጋሊ ድልን ማክበር እንዳቆምነውና ራስ አሉላንም አብረን መዘከር እንዳቆምነው ሁሉ ዓድዋንም ላንዘክር የምንችልበት ጊዜ ይመጣል።
* * * * *
እያንዳንዱ ቦታ ላይ ያስተዋልነውና ያየነው ነገር በሁለት መንገድ የተወጠረ ነው። ከውጪ ያለውና የትግራይን ጉዳይ አንስቶ የሚሟገተው አካል የያዘበት መንገድና መንግስት ጉዳዩን የያዘበት መንገድ ከፍተኛ ውጥረት ያለበት ነው። መሀል ላይ ያለውን ህዝብ ስታይው ግን ከፍተኛ የስነ-ልቦና ጉዳት ላይ መውደቁን ትረጂያለሽ። ከፍተኛ ውድመት የደረሰበት፣ የተዘረፉ ቤቶች፣ የተሰባበሩ እቃዎች ፣ በጥይት የተበሳሱ መስታዎቶች፣ የተዘረፉና ኦና የቀሩ ቤቶችን አይተናል።
* * * * *
በሌላ በኩል፤ ህዝቡን ለማናገር ሞክረን ነበር። እኛንም ይቀበሉን የነበሩ ሰዎች ጋር ለመነጋገር እንደሞከርነው ኢትዮጵያዊነታቸው ላይ ጥያቄ ምልክት እንደፈጠረባቸውና የስነ-ልቦና ጉዳት እንደደረሰባቸው አስተውለናል። በምን ምክንያት ይህ ጉዳት ደረሰባቸው ብትይኝ እኔ ልተነትነው አልችልም። መልሱ ፖለቲካዊ ሊሆን ይችላል። ግን በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብ ሰላም አግኝቷል ብሎ ተረጋግቶ መቀመጥ እንደ ሀገር ዋጋ ያስከፍለናል።
* * * * *
የትግራይን ጉዳይ በአዳዲስ መንገዶችና የመፍትሄ ሀሳቦች፣ እስከዛሬ ባልተካሄደበት አዲስ መንገድ ሰላም መፈጠር አለበት። ይሄንን ከእኛ ውጪ ያሉ ምሁራን፣ ፖለቲከኞችም ሆኑ ማህበራዊ አንቂዎች ቆም ብለው ማሰብ አለባቸው። በምንም ተባለ በምንም ህዝቡ ከደረሰበት የህይወት ጫና፣ የስነ-ልቦና ስብራትና ምስቅልቅል መውጣት አለበት።
https://www.facebook.com/getu26/posts/5479434145430115
