Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11590
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

ድርጅቶች መያዝ የሚችሉት ጥሬ ገንዘብ ከ1.5 ሚሊዮን ወደ 200 ሺሕ ብር ዝቅ ተደረገ - Eritreanizing Ethiopia

Post by sarcasm » 10 Mar 2021, 21:49

ሪፖርተር

10 March 2021
ሳምሶን ብርሃኔ
ግንባታ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች በገደቡ ምክንያት ሥራቸው እንዳይስተጓጎል ተሰግቷል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ድርጅቶች ከባንክ ውጪ ማንቀሳቀስ የሚችሉትን ጥሬ ገንዘብ መጠን ከ1.5 ሚሊዮን ብር ወደ 200 ሺሕ ብር ዝቅ አደረገ።

ከባንክ ውጪ የሚደረጉ የጥሬ ገንዘብ ግብይቶችን ለመቀነስ ያለመው አዲሱ መመርያ፣ ግለሰቦች ማንቀሳቀስ የሚችሉትን የገንዘብ መጠን ከ200 ሺሕ ብር ወደ 100 ሺሕ ብር ዝቅ አድርጎታል።

ከነሐሴ 2012 ዓ.ም. አንስቶ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመርያ መሠረት ድርጅቶች እስከ ከ1.5 ሚሊዮን ብር ድረስ ጥሬ ገንዘብ መያዝ ይችሉ የነበረ ሲሆን፣ ከዚህ ገንዘብ በላይ ይዘው በሚገኙ ቅጣት እንደሚጠልባቸው ተገለጾ ነበር።

በውቅቱ ገደቡ የተቀመጠው ግለሰቦችና ድርጅቶች በቤትና በመሥሪያ ቤቶቻቸው ውስጥ በርካታ ጥሬ ገንዘብ ስለሚያስቀምጡና ይህንን ለማስቀረት እንደነበር ተገልጾ የነበረ ሲሆን፣ ግብር መሰወርና ማጭበርበርንም ያስቀራል ተብሎ ነበር።

በተመሳሳይ ይበልጥኑ ዝቅ የተደረገው አዲሱ ገደብ ጥሬ ገንዘብ ከባንክ ውጪ የማስቀመጥን ልምድ ያስቀራል ተብሎ የታሰበ ቢሆንም፣ እንደ ግንባታና ሌሎች ከፍተኛ ገንዘብ የሚፈልጉ የቢዝነስ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች የሥራ እንቅስቃሴዎቻቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳያሳድር ሥጋታቸውን ከወዲሁ እየገለጹ ነው።

Continue reading