አንዱ ወልቃይትንና ራያን የይመለከታል፡፡ የወልቃይት ጣጣ፤ የራያ እጣ፡፡ የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 48(1) የክልል ወሰንን በሚመለከት ጥያቄ የተነሳ እንደሆነ፤ በሚመለከታቸው ክልሎች ስምምነት ይወሰናል፤ ክልሎቹ ካልተስማሙ ደግሞ፤ የፌዴሬሽን ምክርቤቱ ይወስናል ይላል፡፡ ይሄ የወልቃትና ጠገዴ፤ የራያም ጉዳይ፤ በዚህ መልኩ እንጂ፤ ዛሬ ጉልበት አገኘሁ ተብሎ፤ ለዚያውም በኤርትራ እርዳታ ፤ ጠቅልዬ ልውሰድ ቢባል፤ ብዙ ችግር ያመጣል፡፡
አንደኛ ዘላቂ ሰላም አያሰፍንም፡፡
ሁለተኛ፤ ለሌሎች አካባቢዎችም መጥፎ ምሳሌ ይሆናል (ለምሳሌ አዲስ አበባን፤ የኦሮምያ መንግስት ወሮ የኔ ነው ቢል፤ መከራከር አይቻልም፤ ጉልበቱና አቅሙ እስካለው ድረስ; ሱዳንስ ቢሆን ከዚህ ምን ይማራል፡፡ በጉልበት ይዣለሁ፤ አለቅም ነው የሚል)፡፡
ሶስተኛ፤ ሕወሀቶች ከ30 አመታት በላይ ያደረጉትን መድገም ይሆናል፡፡ እነሱን ጉልበት ከ30 አመታት በላይ አላዛለቃቸውም፡፡ ሀይልና ጡንቻ ብቻውን ዘላቂ ሰላም አያመጣም፡፡ ሕግም ጭምር እንጂ፡፡ (ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ፤ የተራ ጉዳይ እንጂ፤ ሁሉም ጀግና ነው፡፡ የትናንት ጀግና ዛሬ ዋሻ ገብቷል፡፡ ቢያንስ 27 አመታት ግን አንቀጥቅጠው ገዝተውናል፤ እኛም በፍርሀት እየራድን ተገዝተናል)፡፡
አራተኛ፤ የፌደራል መንግስቱንም አጣብቂኝ ውስጥ መክተት ነው፡፡
ስድስተኛ፤ አዲሱን የትግራይ አስተዳደርም ማስፎገር ይሆናል፡፡
ሰባተኛ፤ በርግጥም የተጠቀሱት መሬቶች፤ ወልቃይትም የጎንደር፤ ራያም፤ የወሎ፤ እንጂ በታሪክ የአማራ ክልል ሆነው አያውቁም፤ ምክንያቱም፤ የአማራ ክልል የተፈጠረው፤ በሽግግር መንግስቱ በ1983 በአሁኑ ሕገመንግስት ደግሞ በ1987 ነውና፡፡ ከዚያ በፊት፤ የአማራ ባህል እንጂ፤ የአማራ ክልል የሚባል የት ነበርና፡፡
ጎንደርና ወሎ ክልሎች ሆነው፤ እነዚህ አወዛጋቢ ግዛቶቸ ለነሱ ቢመለሱ፤ ትግሬዎቹም እንዲህ እንዳሁኑ ብዙ የሚያንጨረጭራቸው አይመስለኝም፡፡
በርግጥ፤ ጎንደሬዎቹንም ደም ከፍለውበት፤ ተጎድተውበት፤ ሙሉ በሙሉ ለቃችሁ ውጡና ለትግሬዎቹ ስጡ ማለት ይከብዳል፡፡ Compromise ኢትዮጵየ ውስጥ የሌለ ብርቅዬ ቃል፡፡ ካማራውም፤ ከትግሬውም፤ ከፌደራል መንግስትም የተወጣጣ አካል ያስተዳድረው፡፡ እንጂ፤ የራሱን ሕገ መንግስት የማያከብር መንግስትና ክልል አይጸናም፡፡ እስከዚው ግን፤ ጎንደሮች፤ ባህርዳር ስር ከሚርመጠመጡ፤ የአጼ ፋሲል አገር፤ የቴዎድሮስ ምድር፤ ራሱን ችሎ ክልል ቢሆን፤ ከይህ ሁሉ ይገላግለን ነበር፡፡ ኮቪድ ሲጠፋ፤ ኮለምበስና ሲያተል ተመልሼ ጎንደርን መቀስቀስ ሊኖርብኝ ነው፡፡ Gondar for Statehood, now !!

https://www.facebook.com/tsahlemariam/p ... 7713480943
ነገ ደግሞ፤ የዚህ የኤርትራን ነገር ጾም እይዝበታለሁ፡፡
