Page 1 of 1

በአዲስ አበባ ከተማ ለኑሮ ውድነት ምክንያት ናቸው የተባሉ ከ30 ሺህ በላይ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ (ETV) Eritreanizing Ethiopia .....

Posted: 27 Feb 2021, 20:14
by sarcasm
Please wait, video is loading...
መንግሥትንም የተገዳደረው የዋጋ ግሽበት

20 January 2021



...........በመንግሥት የራሱን ገቢ አስቀርቶና ታክስ ቀንሶ እንዲገቡ የተፈቀዱ ምርቶች ሳይቀሩ ዋጋ ጭማሪ የታየባቸው መሆኑን በመገንዘብ፣ ያላግባብ ጭማሪ ያደረጉ ላይ ዕርምጃ ወስጃለሁ ቢልም ዕርምጃው ለውጥ አላመጣም፡፡

የምግብ ነክ ምርቶች ከ20 በመቶ በላይ ጭማሪ እየታየባቸው ስለመሆኑ በተከታታይ የወጡት የጥቅምትና የኅዳር ወር የብሔራዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ ያመለክታል፡፡ የዋጋ ግሽበት ለዓመታት የቆየ፣ አሁንም እየጨመረ የመጣ ሲሆን፣ የሁኔታው አሳሳቢነትንም በመገንዘብ በመንግሥት ረገድ የተለያዩ ዕርምጃዎች እንዲወሰድ ያስገደደ ሆኗል፡፡

እንደ ንግድ ሚኒስቴር መረጃ፣ በገበያ ውስጥ እጥረት እንዳይፈጠር ተከታታይ ዕርምጃዎች እየተወሰዱ በመሆኑ፣ በተለይ በአሁኑ ወቅት የምርት እጥረት አለ ተብሎ አይታሰብም፡፡

እንዲያውም የአንበጣና የጎርፍ አደጋዎች ያሳረፉት ተፅዕኖ አለ ቢባል እንኳን፣ ከቀደመው ዓመት የተሻለ ምርት እንዳለም እየተጠቀሰ ነው፡፡ ይህም የዋጋ ጭማሪውን ምክንያታዊ አያደርገውም፡፡ በመንግሥት በኩል ዋጋን ለማረጋጋት በተጨባጭ ተሠርቷል የሚባለው ሌላው ሥራ ለአምራችና ለኅብረት ሥራ ማኅበራት 800 ሚሊዮን ብር ብድር ለመስጠትና የምርት አቅርቦትን ለማሳደግ በጀት ስለመያዙ ማስታወቁ ነው፡፡

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እንዳሉትም፣ ይህ ብድር በዋናነት እያሻቀበ ያለውን የዋጋ ግሽበት መፍትሔ ለማበጀትና የኅብረት ሥራ ማኅበራት ያለ ችግር ምርቶችን እንዲያቀርቡ ለማገዝ ታስቦ የተወሰደ ዕርምጃ ነው፡፡

መንግሥት ሌሎች ዕርምጃዎችንም እየወሰደ ሲሆን፣ የዋጋ ግሽበቱ አልተገታም፡፡ ባለሁለት አኃዝ ሆኖ የቀጠለውን የዋጋ ግሽበት ለማረጋጋት የተዋቀረው የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ በቅርቡ እንዳሳወቀውም፣ ለዓመታት አገሪቱን እየተፈታተናት የቆየውን የዋጋ ግሽበት ለማሻሻል የተለያዩ ዕርምጃዎች እየተወሰዱ ቢሆንም፣ ይህ ጉዳይ እንዲህ በቀላሉ ሊፈታ የማይችል መሆኑን የሚጠቁም ነው፡፡

የዋጋ ግሽበት በመንግሥት ደረጃ ፈታኝ ስለመሆኑ ሌላው ማሳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ተጨማሪና ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቀው አንዱ ችግር የዋጋ ግሽበት መሆኑን በቅርቡ መግለጻቸው ነው፡፡ የመንግሥታቸውን የ2013 በጀት ዓመት የመጀመርያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም በተመለከተ በፓርላማ በሰጡት ማብራሪያ፣ የዋጋ ግሽበትን ለማሻሻል አምና በርካታ ሥራ የተሠራና ጥረት የተደረገ ቢሆንም፣ የሚፈለገውን ውጤት እንዳላመጣ ገልጸዋል፡፡

እንደ እርሳቸው እምነት፣ የገንዘብ ለውጡ የሚያመጣው አዎንታዊ ተፅዕኖ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ አሁንም የዋጋ ግሽበቱን ለመቀነስ ሰፊ ሥራ የሚጠይቅና የማክሮ ቡድኑ ራስ ምታት ነው፡፡

ለኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ኢኮኖሚያዊና ኢኮኖሚያዊ ያልሆኑ ምክንያቶች ተደበላልቀው የሚፈጥሩት መሆኑ ችግሩን የሚያከብድ ሆኖ ይታያል፡፡ ይህንን ችግር መንግሥት በሚያወጣቸው ፖሊሲዎች ብቻ በአጭር ጊዜ ለማከም የማይቻል መሆኑን የማክሮ ኮሚቴ መጥቀሱም የችግሩን አሳሳቢነት የሚጠቁም ነው፡፡ የፕላንና ኢኮኖሚ ኮሚሽነሯም ችግሩን ለማቃለል የመዋቅር ለውጥ ያስፈልጋል ይላሉ፡፡

በአጭር ጊዜ የሚፈታ ያለመሆኑንም በመጥቀስ፣ ችግሩ መዋቅራዊ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ብዙ ሥራ እንደሚጠይቅ መግለጻቸውም የዋጋ ግሽበት በእርግጥ ከዚህም በኋላ የመንግሥት ፈተና ሆኖ የሚቀጥል መሆኑን ያሳያል፡፡

የዋጋ ግሽበት አሁንም ሰፊ ሥራና ርብርብ የሚጠይቅ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከዚህ አኳያ የዋጋ ግሽበቱ ገፊ ምንያቶች ምንድናቸው? የሚለውን መዘርዘር በጥልቀት መለየት አንዱ ሥራ ይሆናል ብለዋል፡፡

ችግሩ የማሳሰቡን ያህል ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች ስለመኖራቸውና ተጨማሪ ምርት የሚገኝበት አሠራር በመከተል ውጤት የታየባቸው ስለመሆኑ መንግሥት ይገልጻል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩም፣ የግብርና ምርት የራሱ ፈተና ቢኖረውም ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች ለመኖራቸው አንዱ ማሳያ ብለው የጠቀሱት፣ በመስኖ፣ በኩታ ገጠምና በቴክኖሎጂ ምርት ማሳደግ አንዱ የመፍትሔው አካል በመሆኑ በዚሁ አኳያ እየተሠራ መገኘቱ ነው፡፡

ነገር ግን ምርታማነትን ብቻ ማሳደግ በቂ ያለመሆኑንና የንግድ ሥርዓቱን ማዘመን እንደሚጠይቅም ገልጸዋል፡፡ የንግድ ሥርዓቱ ከፍተኛ ውስንነት ያለበት እንደሆነ ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ፣ ‹‹ወጣ ስትሉ ምርት አለ፡፡ እዚህ ደግሞ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ግሽበት አለ፡፡ ይህንን እንዴት እናገናኛለን የሚለውን ከንግድ ሥርዓቱ በተጨማሪ ሎጂስቲክስ ማዘመን ይፈልጋል፤›› ማለታቸው ይታወሳል፡፡

ለዚህም የመሠረተ ልማት ግንባታ ከፍተኛውን ሚና የሚይዝ ይሆናል፡፡ ፍላጎትና አቅርቦትን ማጣጣምም እንዲሁ፡፡

መንግሥት ዋጋን ለማረጋጋት የወሰዳቸው ዕርምጃዎች ባይኖሩ ኖሮ፣ ከዚህም በላይ የዋጋ ግሽበት ሊከሰት ይችል እንደነበር የሚጠቁሙ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ግን፣ አሁንም መንግሥት በጊዜያዊነት በተለይ መሠረታዊ የሚባሉ ምርቶች ላይ እጁን በማስገባት ማስተካከል ግድ ይለዋል፣ ገበያውንም ሥርዓት ማስያዝ አለበት ይላሉ፡፡

ይህ ግን ዘላቂ መፍትሔ ያለመሆኑን በመጥቀስ ማክሮ ኢኮኖሚው ላይ አሁንም ብዙ ሊሠሩ የሚገባቸው ሥራዎች እንዳሉ ይጠቁማሉ፡፡ መንግሥት ታክስ እየቀነሰ የሚያስገባው ምርት ዋጋው እየጨመረ መምጣቱ የግብይት ሥርዓቱ ችግር መሆኑን፣ እየጨመረ ያለው የውጭ ምንዛሪም የራሱ የሆነ ተፅዕኖ እንዳለው ይጠቁማሉ፡፡

Read the whole article https://www.ethiopianreporter.com/article/21070